loading
የዩኬ ሩብ ዓመታዊ ብድር ከፍተኛ ክብረወሰን አስመዘገበ::

አዲስ አበባ፣ሐምሌ14፣ 2012 የዩኬ ሩብ ዓመታዊ ብድር ከፍተኛ ክብረወሰን አስመዘገበ::የእንግሊዝ መንግሥት የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ በዜጎች ላይ ከፍተኛ የፋይናንስ ጫና እያደረሰ በመሆኑ የእንግሊዝ መንግሥት ከኤፕሪል እስከ ሰኔ ወር ድረስ ብቻ የ127.9 ቢሊዮን ዩሮ ብድር አግኝቷል፡፡  አኃዙ በወጪ እና በግብር ገቢ መካከል ያለው ልዩነት ካለፈው የግብር ዓመት በሙሉ ከተበደረው 55.4 ቢሊዮን ዩሮ እጥፍ ነበር። ሆኖም በሰኔ ወር ውስጥ […]

ወጋገን ባንክ በ2012 በጀት አመት የ46.9 በመቶ እድገት በማሳየት ከታክስ በፊት 1.1 ቢሊዮን ብር አተረፈ::

አዲስ አበባ፣ሐምሌ14፣ 2012 ወጋገን ባንክ በ2012 በጀት አመት የ46.9 በመቶ እድገት በማሳየት ከታክስ በፊት 1.1 ቢሊዮን ብር አተረፈ::ይህም ከባለፈዉ ተመሳሳይ አመት ጋር ሲነፃፀር የ46.9 በመቶ ወይም የ344.7 ሚሊዮን ብር ብልጫ እንዳለዉ ተገልጽዋል፡፡የባንኩ ፕሬዝዳንት አቶ አባይ መሃሪ የባንኩን የ2012 በጀት አመት የስራ አፈፃጸም ላይ ማብራሪያ በሰጡበት ወቅት የኮሮና ወረርሽኝ በኢኮኖሚዉ እንቅስቃሴ ላይ በፈጠረዉ መቀዛቀዝ ምክኒያ በብድር […]

በመዲናዋ “አንድ መምህር ለአንድ ቤተሰብ” በሚል የክረምት ማጠናከሪያ ትምህርት የበጎ ፍቃድ አገልግሎት ተጀመረ::

አዲስ አበባ፣ሐምሌ14፣ 2012 በመዲናዋ “አንድ መምህር ለአንድ ቤተሰብ” በሚል የክረምት ማጠናከሪያ ትምህርት የበጎ ፍቃድ አገልግሎት ተጀመረ::የአዲስ አበባ ከተማ ትምህርት ቢሮ ከወጣቶች እና የበጎ ፍቃድ ማስተባበሪያ ቢሮ እንዲሁም የግል ትምህርት ቤቶች ማህበር ጋር በመተባበር ነው መርሃ ግብሩን የጀመረው። ይፋ በተደረገው የክረምት ማጠናከሪያ ትምህርት የበጎ ፍቃድ አገልግሎት መርሃ ግብር ላይ የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ የሰራ ኃላፊዎች፣ የከተማው […]

የዓለም ጤና ድርጅት አሁንም የአፍሪካ ጉዳይ እንደሚያሳስበው ገለፀ::

አዲስ አበባ፣ሐምሌ14፣ 2012 የዓለም ጤና ድርጅት አሁንም የአፍሪካ ጉዳይ እንደሚያሳስበው ገለፀ:: የድርጅቱ የአስከቸኳይ የጤና ነክ ጉዳዮች ሀላፊ የሆኑት ሚካኤል ሪያን በሰጡት መግለጫ መላው አፍሪካ የደቡብ አፍሪካን ሁኔታ ተመልክቶ መጠንቀቅ አለበት ሲሉ አሳስበዋል፡፡ ደቡብ አፍሪካ ከ373 ሺህ በላይ ሰዎች በቫይረሱ ሲያዙባት ከ5 ሺህ በላይ ዜጎቿ በኮቪድ19 ሳቢያ ህይታቸው አልፏል፡፡ በመጀመሪያ አካባቢ ሀብታም በሆኑ የአፍሪካ ሀገራት የጀመረው […]

በኢትዮጵያ መንገዶች በሚገባዉ መልኩ ጥገና እየተካሄደላቸዉ ባለመሆኑ ሀገሪቱን ለክስረት እየዳረጋ መሆኑን የመንገድ ፈንድ ፅ/ቤት ለአርትስ ተናገረ፡፡

አዲስ አበባ፣ሐምሌ14፣ 2012 በኢትዮጵያ መንገዶች በሚገባዉ መልኩ ጥገና እየተካሄደላቸዉ ባለመሆኑ ሀገሪቱን ለክስረት እየዳረጋ መሆኑን የመንገድ ፈንድ ፅ/ቤት ለአርትስ ተናገረ፡፡ የመንገድ ፈንድ ፅ/ቤት ከዛሬ 23 ዓመታት በፌት መንገዶች ተገንብተዉ በሚገባዉ መልኩ ጥገና እንዲደረግላቸዉና የመንገዶችን እድሜ ለማራዘም ታስቦ በ1989 ዓ.ም  የተቋቋመ ቢሆንም በተቋቋመበት ጊዜ ሂሳብ ዛሬ ድረስ ፈንድ በመደረጉ የሀገሪቱ መንገዶች በሚገባ እንዳይጠገኑ ከማድረጉም በላይ ለከፍተኛ ኪሳራ […]

በጉራጌ ዞን በድምቀት የሚከበሩ የሀይማኖትና ባህላዊ በዓላት ህዝቡ ባሉበት እንዲያከብሩ መወሰኑን የዞኑ ግብረ ሃይል አስታወቀ፡፡

አዲስ አበባ፣ሐምሌ15፣ 2012 በጉራጌ ዞን በድምቀት የሚከበሩ የሀይማኖትና ባህላዊ በዓላት ህዝቡ ባሉበት እንዲያከብሩ መወሰኑን የዞኑ ግብረ ሃይል አስታወቀ፡፡በጉራጌ ዞን ኮቪድ መከላከል እና መቆጣጠር ግብረ ሃይል የአረፋ በአልን አስመልክቶ ለአርትስ በላከዉ መግለጫ እንዳስታወቀዉ ፤የኮቪድ 19 በሀገራችን ከተከሰተ ጀምሮ ወረርሽኙን በመከላከል ፤ በመቆጣጠር ግብረሃይሉ ጥረት እያደረገ እንደሆነ ገልጸዋል፡፡ግብረ ሃይሉ በሌላ መልኩ ከአርሶ አደር ከመንግስት ሰራተኛ ከባለሃብትና ሌሎች […]

አልበሽር ከ30 ዓመታ በፊት ፈፀሙት በተባለ የመፈንቅለ መንግስት ክስ ፍርድ ቤት ቀረቡ::

አዲስ አበባ፣ሐምሌ15፣ 2012 አልበሽር ከ30 ዓመታ በፊት ፈፀሙት በተባለ የመፈንቅለ መንግስት ክስ ፍርድ ቤት ቀረቡ:: የቀድሞው የሱዳን ፕሬዚዳንት ኦማር ሀሰን አልበሽር እንደ አውሮፓዊያኑ አቆጣጠር በ1989 በዲሞክራሲያዊ መንገድ የተመረጠውን የጠቅላይ ሚኒስትር ሰዲቅ አል መሃዲን መንግስት በሃይል ገልብጠዋል ተብለው ነው ክስ የተመሰረተባቸው፡፡አፍሪካ ኒውስ እንደዘገበው አልበሽር በተከሰሱበት የመፈንቅለ መግስት ወንጀል ጥፋተኛ ሆነው ከተገኙ የሞት አልያም የእእድሜ ልክ እስር […]

የኢትዮጵያ አየር መንገድ እቃ ጫኝ አውሮፕላን በሻንጋይ አውሮፕላን ማረፊያ ውስጥ እቃ በሚጭነበት ወቅት በእሳት መያያዙ ተሰማ::

አዲስ አበባ፣ሐምሌ15፣ 2012 የኢትዮጵያ አየር መንገድ እቃ ጫኝ አውሮፕላን በሻንጋይ አውሮፕላን ማረፊያ ውስጥ እቃ በሚጭነበት ወቅት በእሳት መያያዙ ተሰማ::አየር መንገድ እቃ ጫኝ አውሮፕላን በቻይና ሻንጋይ አውሮፕላን ማረፊያ ውስጥ እቃ በሚጭነበት ወቅት ነዉ በእሳት የተያያዘዉ።ሁሉም የአውሮፕላኑ ሰራተኞ በመልካም ደህንነት ላይ እንደሚገኙ የኢትዮጵያ አየር መንገድ አስታውቋል።አየር መንገዱ አደጋውን አስመልክቶ ባወጣው መግለጫ ቦይንግ 777 ኢቲ ኤአርኤች እቃ ጫኝ […]

ቢሮዉ ለሞተር ሳይክሎች ከዚህ በኋላ ፍቃድ እንደማይሰጥ ገለፀ::

አዲስ አበባ፣ሐምሌ15፣ 2012 ቢሮዉ ለሞተር ሳይክሎች ከዚህ በኋላ ፍቃድ እንደማይሰጥ ገለፀ::በአዲስ አበባ ከተማ በሞተር ሳይክሎች ላይ የወጣዉን መመሪያ በመጣስ ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ሞተኞች ላይ እርምጃ እየወሰደ መሆኑን የ ከተማ አስተዳደሩ ትራንስፖርት ቢሮ አስታወቀ፡፡በከተማዋ ነዋሪ የነበሩና በሞተር ሳይክል ላይ ኑሮአቸዉን አድርገዉ ህጋዊ ለሆኑ 3600 የሚሆኑ ሞተረኞች ፋቃድ መስጠቱን ያስታወቀዉ ቢሮዉ ፋቃድ ከተሰጣቸዉ ዉጪ የሚንቀሳቀሱ ግን ንብረታቸዉ ተወርሶ […]

ግብፅ በታሪኳ እንደዚህ አይነት ፈተና ገጥሟት አያውቅም አሉ የግብጽ ጠቅላይ ሚኒስትር ሙስጠፋ ማድቡሊ::

አዲስ አበባ፣ሐምሌ16፣ 2012 ግብፅ በታሪኳ እንደዚህ አይነት ፈተና ገጥሟት አያውቅም አሉ የግብጽ ጠቅላይ ሚኒስትር ሙስጠፋ ማድቡሊ::             ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህን ያሉት በቅርቡ በተመሰረተችው አዲሷ አልኣሚ ከተማ ሚንስትሮችን ሰብስበው በመንግስት አጀንዳዎች ዙሪያ ባወያዩበት ወቅት ነው፡፡ሀገራችን ከውጭም ከውስጥም እንደዚህ አይነት ፈተና ገጥሟት አያውቅም ያሉት ማድቡሊ በተለይ በሲናይ በረሃ ሽብርተኝነትን ለመዋጋት ብዙ ውጣ ውረዶች […]