loading
በአዲስ አበባ ትላንት በተከሰተ የጎርፍ አደጋ ከአንድ ቤተሰብ 5 ሰዎች ህይወታቸዉ አልፏል-ተጎጂዎች

አዲስ አበባ፣ ነሃሴ 12፣2013  በመዲናዋ ትናንት በተከሰተ የጎርፍ አደጋ እስካሁን የ7 ሰዎች ህይወት አለፈ:: የአዲስ አበበ እሳትና ድንገተኛ አደጋዎች ስራ አመራር ኮሚሽን ኮሚሽነር ሰለሞን ፍሰሃ ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት እንደገለጹት÷ በተከሰተው አደጋ በህይወት እና ንብረት ላይ የደረሱ ጉዳቶች እየተጣሩ ነው፡፡ እስካሁን በአደጋው የ7 ሰዎች ህይወት ማለፉን የገለጹት ኮሚሽነሩ÷አጠቃላይ የደረሰው ጉዳት ዛሬ ከሰዓት ይፋ እንደሚደርግም ጠቁመዋል፡፡ በመካነየሱስ […]

በሳዑዲ አረቢያ እስርቤቶች የሚገኙ ኢትጵያዊያን ወደ ሀገራቸው ሊመለሱ ነው፡፡

አዲስ አበባ፣ ነሃሴ 12፣2013 በሳዑዲ አረቢያ የተለያዩ ማቆያ ማእከላትና እስር ቤቶች የሚገኙ ኢትዮጵያዊያን ከዚህ ሳምንት ጀምሮ ወደ ሀገራቸው እንደሚመለሱ ተገለፀ፡፡ የዉጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ጽ/ቤት በሪያድ የሚገኘነውን የኢትዮጵያ ኤምባሲን ጠቅሶ በፌስቡክ ገጹ እንዳሰፈረው፤ የኢትዮጵያ መንግስት ከሳዑዲ አረቢያ መንግስት ጋር በመቀናጀት በሳምንት ሶሶት በረራዎችን በማድርግ በሳዑዲ አረቢያ የተለያዩ ማቆያ ማዕከላትና እስር ቤቶች የሚገኙ ዜጎችን ከዚህ […]

በኒውዚላንድ አንድ የኮቪድ-19 ተጠቂ መገኘቱን ተከትሎ በሀገር አቀፍ ደረጃ ዕቀባ ተጣለ፡፡

አዲስ አበባ፣ ነሃሴ 12፣2013 በኒውዚላንድ አንድ የኮቪድ-19 ተጠቂ መገኘቱን ተከትሎ በሀገር አቀፍ ደረጃ ገደብ መጣሉ ተነገረ፡፡በኒው ዚላንድ በስድስት ወር ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ፤ ኦክላንድ ውስጥ አንድ ሰው የኮቪድ-19 ተህዋሲ ተጠቂ መሆኑን ሪፖርት መደረጉን ተከትሎ ከሶስት ቀን እስከ ሳምንት የሚደርስ የእንቅስቃሴ ገደብ መጣሉ ታውቋል። በተህዋሲው የተያዘው ሰው የተጎበኘችው የባህር ዳርቻዋ ከተማ ኮሮማንዴል እንደ ኦክላንድ ሁሉ ለሰባት ቀናት […]

51 ሺህ 89 ኢትዮጵያዊያን ከሀገር ወጥተው የት እንዳሉ አይታወቅም::

አዲስ አበባ፣ ነሃሴ 12፣2013 ከሀገር ውጪ ፈልሰው አድራሻቸው ያልታወቁ 51 ሺ 89 ዜጎች መኖራቸውን የማዕከላዊ ስታቲስቲክስ ኤጀንሲ አስታወቀ፡፡ ኤጀንሲው የአለማቀፍ ፍልሰት ድርጅት እና ዳኒሽ ከተባለ ግብርሰናይ ድርጅት ጋር በመተበባር ባስጠናው ጥናት 51 ሺ 89 ኢትዮጵያዊያን ከሀገር እንደወጡ የት እንዳሉ እንዳልታወቀ ደርሼበታለሁ ብሏል፡፡ ከ41 ሺህ በላይ ቤተሰቦች ለተካተቱበት ለዚህ ጥናት የኢትዮጵያ መንግስት 36 ሚሊዮን ብር ያወጣበት […]

በአፍጋኒስታን ጉዳይ አሁንም አቋሜ የጸና ነው -ጆ ባይደን

አዲስ አበባ፣ ነሃሴ 12፣2013  የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ጆ ባይደን ከአፍጋኒስታን ወታደሮቼን በማውጣት ውሳኔዬ የምጸጸትበት አይደልም ሲሉ ተናገሩ፡፡ አንድም የአሜሪካ ወታደር በአፍጋኒሰታን ምድር ሊሞት አይገባም ያሉት ባይደን በአወጣጥ ላይ ክፍተቶች እንደነበሩ አልሸሸጉም፡፡ ጆ ባይደን ማስተባበያ በሰጡበት በዚህ ንግግራቸው እንዳብራሩት፣ የአፍጋኒሰታን ጦር ታሊባንን ለመዋጋት ፍላጎት እንዳልነበረው፤ የአፍጋኒሰታን መንግሥትም ወዲያውኑ ተስፋ እንደቆረጠ ከገለጹ በኋላ ፤ታሊባን ካቡልን ይቆጣጠራል ብለን ከገመትንበት […]

የቱርክ የፊልም ኢንዱስትሪም የህዝብ ለህዝብ ግንኙነትን እያጠናከረ ነው-ጠ/ሚ ዐቢይ::

አዲስ አበባ፣ ነሃሴ 13፣2013 የለውጥ ሂደቱ ከጀመረበት ጊዜ አንስቶ ኢትዮጵያና ቱርክ ግንኙነታቸውን ለማጠናከር በጋራ እየሰሩ ነው:: ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ገለጹ፡፡ ኢትዮጵያና ቱርክ የሁለትዮሽ ግንኙነታቸውን ማጠናከር የሚያስችሉ ተጨማሪ  ስምምነቶችን ተፈራርመዋል። በቱርክ የስራ ጉብኝት እያደረጉ የሚገኙት ጠቅላይ ሚኒስትር አቢይ አህመድ ከቱርኩ ፕሬዚዳንት ሬሲፕ ጣይብ ኤርዶጋን ጋር በመሆን መግለጫ ሰጥተዋል። ፕሬዚዳንት ኤርዶጋን በመግለጫቸው ሁለቱ አገሮች ያላቸው ግንኙነት ወንድማማችነት ነው ብለዋል፡፡ በጠቅላይ ሚኒስትሩ በሚመራው […]

ህወሓትን ሲደግፉ የነበሩ ግለሰቦችን ለህግ ለማቅረብ ከኢንተርፖል ጋር እየሰራን ነዉ-ፌደራል ፖሊስ::

አዲስ አበባ፣ ነሃሴ 13፣2013  ለአሸባሪው ህወሓት የኢኮኖሚ ምንጭ ሆነው ሲያገለግሉ የቆዩ 117 የንግድ ድርጅቶች እና መኖሪያ ቤቶች ላይ ህጋዊ እርምጃ መውሰዱን የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ። ኮሚሽኑ ህገወጥ ምንዛሪን አስመልክቶ ለአርትስ በላከው መግለጫ እንዳስታወቀው ባካሄደው የተቀናጀ ኦፕሬሽን ለሽብር ቡድኑ የኢኮኖሚ ምንጭ በመሆን ሲያገለግሉ የነበሩ የንግድ ድርጅቶች እና መኖሪያቤቶች ላይ ህጋዊ እርምጃ በመውሰድ የአሸባሪው ቡድን የፋይናንስ ምንጭ […]

በዋሽንግተን ዲሲና አካባቢው የሚገኙ ታዳጊዎች የቡሄ በዓልን በማስመልከት ለህዳሴ ግድብ ገንዘብ አሰባሰቡ፡፡

አዲስ አበባ፣ ነሃሴ 13፣2013  በዋሽንግተን ዲሲና አካባቢው የሚገኙ ታዳጊ ኢትዮጵያዊያን የቡሄ በዓልን በማስመልከት ለታላቁ ህዳሴ ግድብ የገቢ ማሰባሰቢያ ፕሮግራም አካሄዱ በፕሮግራሙ ላይም በቡሄ ጭፈራ የታጀቡ መልዕክቶችን አስተላልፈዋል፡፡ ታዳጊዎቹ ካስተላለፏቸዉ መልዕክቶች ውስጥ የግድቡ መጠናቀቅ ህጻናትና ታዳጊዎች ትምህርታቸውን በአግባቡ በመከታተል የተሻለ ሕይወት እንዲመሩ ያስችላቸዋል የሚለው ይገኝበታል፡፡ በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው መረጃውን ያጋሩት በአሜሪካ የኢትዮጵያ አምባሳደር ፍፁም አረጋ የሁሉም […]

የአሸባሪው ጌታቸው ረዳ ወንድም ሃይለ ረዳ መልዕክት፡፡

አዲስ አበባ፣ ነሃሴ 14፣2013 አሸባሪው ህወሓት ኢትዮጵያን አፈርሳለሁ እንቅስቃሴ የአገር ክህደት መሆኑን የጌታቸው ረዳ ወንድም ሃይለ ረዳ ገለጹ:: በአፋር ክልል ሰመራ ዩኒቨርሲቲ የስነ ዜጋ መምህሩ ሃይለ ረዳ፤ አሸባሪው ህወሓት የትግራይ ን ህዝብ ከአጎራባች ክልሎች ጋር ደም ለማቃባት ትንኮሳ ማድረጉ ፍፁም ተቀባይነት የለውም ሲሉም ገልጸዋል። የሽብር ቡድኑ የአገር ዳር ድንበር የሚጠብቀውን የአገር መከላከያ ሰራዊት ሰሜን ዕዝን […]

የትግራይ ህዝብ ኢትዮጵያን የሚያጸኑ እንጂ የሚያፈርሱ ሀይሎች አካል አይደለም፡፡

አዲስ አበባ፣ ነሃሴ 14፣2013 የትግራይ ህዝብ ኢትዮጵያን የሚያጸኑ እንጂ የሚያፈርሱ ሀይሎች አካል አይደለም፡፡ ኢትዮጵያን ለማፍረስ የውስጥም ሆነ የውጭ ሀይሎች ሲንቀሳቀሱ የትግራይ ህዝብ የመጀመሪያ ከለላ መሆኑን የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ዋና ስራ አስፈፃሚ ዶክተር አብርሃም በላይ ገለጹ፡፡ በአዲስ አበባ የሚኖሩ የትግራይ ተወላጆች በቦሌ ክፍለ ከተማ ተገኝተው ደም በመለገስ ለመከላከያ ሰራዊት ያላቸውን ድጋፍ ገልጸዋል። ዶክተር አብርሃም በላይ […]