loading
የሕክምና ፍቃድ ሳይኖረው የኮቪድ-19 ሕክምና ሲሰጥ የነበረው ግለሰብ ተያዘ፡፡

አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 5፣ 2013 የሕክምና ፍቃድ ሳይኖረው የኮቪድ-19 ሕክምና ማዕከል በመክፈት አገልግሎት እየሰጠ የነበረ ተጠርጣሪ በቁጥጥር ስር ዋለ፡፡ በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 2 ጃፓን ኤምባሲ አካባቢ በሕገ-ወጥ መንገድ የሕክምና ፍቃድ ሳይኖረው የኮቪድ-19 ሕክምና ማዕከል በመክፈት አገልግሎት እየሰጠ የነበረ ተጠርጣሪ በቁጥጥር ስር መዋሉን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታወቀ። የአየር መንገድ አካባቢ ፖሊስ ጣቢያ ከቦሌ ክፍለ ከተማ […]

የገባናቸውን ቃልኪዳኖች ታማኞች ከሆንን የኢትዮጵያን ድል እናበስራለን-ጠ/ሚ ዐቢይ አህመድ

አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 5፣ 2013  የገባናቸውን ቃልኪዳኖች ታማኞች ከሆንን የኢትዮጵያን ድል እናበስራለን ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስቴር ዐቢይ አህመድ ገለፁ ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በንግግራቸውም የተናገሩት ከሚጠፋ የወለዱት ይጥፋ በሚል ማኅበረሰብ ውስጥ ነው ያደግነው ቃል ኪዳን የዓለም ህልውና የተመሠረተበት ሥርዓት ነው ሰው ከሰው ሰው ከአካባቢው አካባቢ እርስ በርሱ ተጠባብቆና ተግባብቶ የሚኖረው በቃል ኪዳን ነው ብለዋል፡፡ ድል የገቡትን ቃል […]

ዓባይ ፀበላችን መብራታችን ለነፍስ ለስጋችንም የሚጠቅመን ሕይወታችን ነው-ብፁዕ አቡነ ናትናኤል::

አዲስ አበባ፣ መስከረም 3፣ 2014 ዓባይ ፀበላችን መብራታችን ለነፍስ ለስጋችንም የሚጠቅመን ሕይወታችን ነው ሲሉ ብፁዕ አቡነ ናትናኤል ገለፁ፡፡የታላቁ ሕዳሴ ግድብን ግንባታን በስፍራው ተገኝተው ለመጀመሪያ ጊዜ ግድቡን የተመለከቱት የምዕራብ ሸዋና ምስራቅ ወለጋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብጹዕ አቡነ ናትናኤል ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ ታላቁ የሕዳሴ ግድብ ኢትዮጵያን ከጨለማ ወደ ብርሃን እና ወደ ከፍታ የምትወጣበት፣ ኢትዮጵያዊያንን ያለምንም ልዩነት […]

በባህሬን ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ከ10 ሺህ የአሜሪካን ዶላር በላይ የቦንድ ግዥ ተፈጸመ::

አዲስ አበባ፣ መስከረም 3፣ 2014  በባህሬን ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ከ10 ሺህ የአሜሪካን ዶላር በላይ የቦንድ ግዥ ተፈጸመ:: የኢትዮጵያ አዲስ ዓመትም ቆንስላ ጀኔራል ጽ/ቤት አምባሳደር ጀማል በከር፣ ዲፐሎማቶችና ሰራተኞች፣ የኃይማኖት መሪዎች፣ በባህሬን የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያንና ትውልደ ኢትዮጰያዊያን በተገኙበት ተከብሯል። አምባሳደር ጀማል በከር ለኢትዮጵያዊያንና ትውልደ ኢትዮጵያዊያን የእንኳን አደረሳቸሁ መልዕክት አስተላልፈዋል። አዲሱ ዓመት የሰላም፣ የደስታ፣ የፍቅር፣ የብልጽግናና ስኬት […]

በአማራ ክልል በአሸባሪው ህወሓት ወረራ ምክንያት ከ260 በላይ ትምህርት ቤቶች ሙሉ ለሙሉ ወደሙ፡፡

አዲስ አበባ፣ መስከረም 3፣ 2014 በአማራ ክልል በአሸባሪው ህወሓት ወረራ ምክንያት ከ260 በላይ ትምህርት ቤቶች ሙሉ ለሙሉ ወደሙ፡፡ በአሸባሪው የህወሓት ወረራ ምክንያት ከ260 በላይ ትምህርት ቤቶች ሙሉ በሙሉ ሲወድሙ 2 ሺህ 511 የሚደርሱ ትምህርት ቤቶች ደግሞ በከፊል ጥቃት እንደደረሰባቸው የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ አስታወቀ፡፡ በአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ የሕዝብ ግንኙነት እና ጽሕፈት ቤት ሀላፊ አቶ […]

አሸባሪው ቡድን ያደረሰው ውድመት በጦር ወንጀል የሚያስጠይቀው ነው -ጎንደር ዩኒቨርስቲ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 3፣ 2014  አሸባሪ ቡድኑ በደቡብ ጎንደር ያደረሰው ሰብዓዊና ቁሳዊ ውድመት በጦር ወንጀል የሚያስጠይቀው ነው ሲሉ በጎንደር ዩኒቨርሲቲ የህግ ትምህርት ቤት ኃላፊ አቶ ልጅ አለም ጋሻው ገለጹ፡፡ በጎንደር ዩኒቨርሲቲ የህግ ትምህርት ቤት ኃላፊና በደቡብ ጎንደር አሸባሪው ቡድን ያደረሰውን ሰብዓዊና ቁሳዊ ውድመት የሚያጣራው የጥናት ግብረ ኃይል ሰብሳቢ አቶ ልጅ አለም ጋሻው ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት […]

የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን ኮሚሽነር ዶ/ር ዳንኤል በቀለ የጀርመን-አፍሪካ 2021 ሽልማት አሸናፊ ሆኑ፡፡

አዲስ አበባ፣ መስከረም 5፣ 2014  የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን ኮሚሽነር ዶ/ር ዳንኤል በቀለ የጀርመን-አፍሪካ 2021 ሽልማት አሸናፊ ሆኑ፡፡ ኢሰመኮ ለአርትስ በላከው መግለጫ እንዳስታወቀው የጀርመን-አፍሪካ ፋውንዴሽን (DAS) ዛሬ መስከረም 5 ቀን 2013 ዓ.ም. ባወጣው መግለጫ፣ የሽልማቱን እጩዎችን የሚያወዳድረው ኮሚቴ ዶ/ር ዳንኤል በቀለ  በጀርመን አገር በአይነቱ ከፍተኛ ለሆነው ሽልማት ሲመርጣቸው በሙሉ ድምጽ እንደሆነ ገልጿል፡፡ ሽልማቱ ዋና ኮሚሽነሩ […]

አዲስ የመንግሥት ተሿሚዎች ስራ ከመጀመራቸው በፊት ሃብት እንዲያስመዘግቡ የሚደረግ መሆኑን የፌዴራል የስነ-ምግባር እና ፀረሙስና ኮሚሽን አስታወቀ።

አዲስ አበባ፣ መስከረም 5፣ 2014 አዲስ የመንግሥት ተሿሚዎች ስራ ከመጀመራቸው በፊት ሃብት እንዲያስመዘግቡ የሚደረግ መሆኑን የፌዴራል የስነ-ምግባር እና ፀረሙስና ኮሚሽን አስታወቀ። ኮሚሽኑ በ2013 ዓ.ም የሃብት ምዝገባ አፈፃፀም እና የ2014 ዓ.ም እቅድን በተመለከተ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል። የኮሚሽኑ የሃብት ማሳወቅ እና ምዝገባ ዳይሬክተር መስፍን በላይነህ፤ በተጠናቀቀው ዓመት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊዮን በላይ የህዝብ ተመራጮች፣ የመንግስት ተሿሚዎች እና […]

የአሜሪካ መንግስት ለኢትዮጵያ ከ3 መቶ ሺህ ባላይ የጆንሰን ኤንድ ጆንሰን የኮቪድ -19 ክትባቶችን ለገሰ::

አዲስ አበባ፣ መስከረም 5፣ 2014 የአሜሪካ መንግስት ለኢትዮጵያ ከ3 መቶ ሺህ ባላይ የጆንሰን ኤንድ ጆንሰን የኮቪድ -19 ክትባቶችን ለገሰ:: በኢትዮጵያ የአሜሪካ ኤምባሲ እንዳስታወቀው አሁን የተለገሰው ክትባት አሜሪካ በቅርቡ ከለገሰችው 1ነጥብ 6 ሚሊዮን ዶዝ ተጨማሪ ሲሆን ፤ይህም ለአፍሪካ ቃል ከተገባው 25 ሚሊዮን ህይወት አዳኝ ክትባት አካል ነው ተብሏል፡፡ የአሜሪካ መንግስት የክትባቶችን ስርጭት በተመለከተ ከአፍሪካ ህብረትና ከአፍሪካ […]