loading
በዐቢይ ፆም ወቅት ሰላም፣ ፍቅር፣ ይቅር ባይነት መታዘዝና አካፍሎ መብላትን መተግበር እንደሚገባ ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ገለፁ፡፡

አዲስ አበባ፣የካቲት 29፣ 2013 በዐቢይ ፆም ወቅት ሰላም፣ ፍቅር፣ ይቅር ባይነት መታዘዝና አካፍሎ መብላትን መተግበር እንደሚገባ ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ገለፁ፡፡ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ፓትርያርክ ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ በዐቢይ ፆም ወቅት ሰላም፣ ፍቅር፣ ስምምነት፣ ይቅር ባይነት መታዘዝና አካፍሎ መብላትን ምዕመኑ መተግበር እንደሚገባው ጥሪ አቅርበዋል፡፡ ፓትርያርኩ የዐቢይ ጾም መግባትን ምክንያት በማድረግ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡ በመግለጫቸውም […]

ለሴቶች ከፍ ያለ ደረጃ መድረስ ከትምህርት ሌላ ምንም መሰላል እንደሌለ ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ ገለጹ ፡፡

አዲስ አበባ፣የካቲት 29፣ 2013 ለሴቶች ከፍ ያለ ደረጃ መድረስ ከትምህርት ሌላ ምንም መሰላል እንደሌለ ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ ገለጹ ፡፡ ሴቶች በትምህርታቸው ውጤታማ በመሆን ከፍተኛ የሃላፊነት ቦታዎችን በብቃት መምራት እንደሚችሉ አምነው እንዲማሩ ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ መክረዋል።ፕሬዚዳንቷ  ዓለም አቀፉን የሴቶች ቀን ምክንያት በማድረግ የቱሉ ዲምቱ ሁለተኛና መሰናዶ ትምህርት ቤትን ጎብኝተዋል። በጉብኝታቸው ከትምህርት ቤቱ የስርዓተ ጾታ ክበብ አባላት ጋር […]

በህዳሴው ግድብ ግንባታና የውሃ አሞላል ሂደት ዙሪያ በትብብር ለመስራት ያሉ ፈተናዎችና መልካም አጋጣሚዎች ላይ ያተኮረ ውይይት ተካሄደ ፡፡

አዲስ አበባ፣የካቲት 29፣ 2013 በህዳሴው ግድብ ግንባታና የውሃ አሞላል ሂደት ዙሪያ በትብብር ለመስራት ያሉ ፈተናዎችና መልካም አጋጣሚዎች ላይ ያተኮረ ውይይት ተካሄደ ፡፡ የውይይቱ ዓላማ በግድቡ ዙሪያ በእውነታ ላይ የተመሰረተና ትክክለኛ መረጃን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ማስተላለፍ ነው ተብሏል፡፡ ውይይቱ በዌብናር የተካሄ ሲሆን በውይይተቱ ከተሳተፉት መካከል በሀገር ውስጥና በአሜሪካን ሀገር የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን እንዲሁም አሜሪካዊያን ይገኙበታል፡፡ ተወያዮቹ በዋናነት […]

በኢኳቶሪያል ጊኒ በአንድ ወታደራዊ ካምፕ በደረሰ ፍንዳታ 20 ሰዎች ሲሞቱ በርካታ ሰዎች ቆስለዋል፡፡

አዲስ አበባ፣የካቲት 29፣ 2013 በኢኳቶሪያል ጊኒ በአንድ ወታደራዊ ካምፕ በደረሰ ፍንዳታ 20 ሰዎች ሲሞቱ በርካታ ሰዎች ቆስለዋል፡፡ በወታደራዊ ካምፑ ላይ አራት ከፍተኛ ፍንዳታዎች መድረሳቸው የታወቀ ሲሆን ከሞቱት 20 ሰዎች በተጨማሪ 600 የሚሆኑት ደግሞ መቁሰላቸው ተሰምቷል፡፡ ፍንዳታው የደረሰው የኢኮኖሚ ከተማ በሆነችው ባታ ከተማ አቅራቢያ በሚገኘው ንኮማ ንቶማ ወታደራዊ ካምፕ ነው፡፡ የፍንዳታው መንስኤ በአካባቢው የሚገኙ አርሶ አደሮች […]

በአሜሪካ በኮቪድ-19 ሳቢያ የሚሞቱ ሰዎች ቁጥር ከወራት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ መቀነሱ ተሰማ፡፡

አዲስ አበባ፣የካቲት 30፣ 2013 በአሜሪካ በኮቪድ-19 ሳቢያ የሚሞቱ ሰዎች ቁጥር ከወራት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ መቀነሱ ተሰማ፡፡ ከሶስት ወር ተኩል በኋላ በአሜሪካ በየቀኑ የሚሞቱት ሰዎች ቁጥር ከ1 ሺህ በታች ሆኖ መመዝገቡን ጆን ሆፕኪንስ ዩኒቨርሲቲ ይፋ አድርጓል፡፡ ለአሜሪካዊያን በ24 ሰዓታት ውስጥ በቫይረሱ የሞቱ ሰዎች 749 ብቻ መሆናቸው ከወራት በኋላ የተሰማ መልካም ዜና ሆኗል፡፡ ፍራንስ 24 እንደዘገበው 10 […]

የኒጄሩ ፕሬዚዳንት ማማዱ ኢሱፎ የ2020 የሞ ኢባራሂም ሽልማት አሸነፉ::

አዲስ አበባ፣የካቲት 30፣ 2013 የኒጄሩ ፕሬዚዳንት ማማዱ ኢሱፎ የ2020 የሞ ኢባራሂም ሽልማት አሸነፉ:: ኢሱፉ ሽልማቱን ያገኙት በሀገራቸው የተከሰቱ በርካታ ችግሮች በቁርጠኝነት በመጋፈጥ ለህዝባቸው ጠቃሚ ስራ ሰርተዋል በሚል ነው፡፡ በተለይ በኒጄር ነፍጥ አንግበው ሽብር የሚፈጥሩ ሀይሎችን በመዋጋት፣ በርሃማነትን በመከላከል የልማት ስራዎችን በመስራት ረገድ አመርቂ ውጤት አስገኝተዋል ነው የተባለው፡፡ ፕሬዚዳንት ኢሱፉ ሀገራቸውን ለ10 ዓመት ካገለገሉ በኋላ ስልጣናቸውን […]

በሀገራችን ያለውን የአይን ህክምና ዘርፍ ከፍ የሚያረግ እና የተሻለ ህክምና የሚገኝበት ላቪስታ የአይን ህክምና ክሊኒክ ተመርቆ ስራ ጀመረ::

አዲስ አበባ ፣ መጋቢት 6 ፣ 2013 በሀገራችን ያለውን የአይን ህክምና ዘርፍ ከፍ የሚያረግ እና የተሻለ ህክምና የሚገኝበት ላቪስታ የአይን ህክምና ክሊኒክ ተመርቆ ስራ ጀመረ:: ላቪስታ የአይን ህክምና በሀገራችን ያለውን የአይን ህክምና ዘርፍ ለማገዝና በተሻለ ለመስራት መቋቋሙ ተነግሯል፡፡ እንዲሁም በአዳዲስ የአይን ህክምና መሳሪያዎች በመታገዝ ታካሚዎች የተሻሉ የተባሉ መሳሪያዎች ለማግኘት ወደ ውጪ ሀገር ሄደው ለመታከም የሚገደዱበትን […]

በናይጄሪያ 30 ወታደሮች በእስላማዊ ታጣቂ ሀይሎች መገደላቸዉ ተሰማ::

አዲስ አበባ ፣ መጋቢት 6 ፣ 2013 በናይጄሪያ 30 ወታደሮች በእስላማዊ ታጣቂ ሀይሎች መገደላቸዉ ተሰማ:: በሰሜን ምስራቅ ናይጄሪያ በ4ቀናት ዉስጥ በእስለማዊ ታጣቂ ሀይሎች ወደ 30 የሚጠጉ ወታደሮች መገደላቸዉን ወታደራዊና ሚሊሻ ምንጮች ገልፀዋል ፡፡ ጥቃቱ በናይጄሪያ የሰሜን ምስራቅ ክፍልን ጨምሮ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የፀጥታዉ ሁኔታ እየተባባሰ መምጣቱን ያስመሰከረ ነዉም ተብሏል ፡፡ በአራቱ ቀናት በተፈፀመዉ ጥቃት 27 […]

የአሜሪካ ጦር የሞዛምቢክ ባህር ሃይል የጂሃዲስቶችን አመጽ ለመውጋት ያግዘው ዘንድ ሊያሰለጥን መሆኑ ተነገረ ፡፡

አዲስ አበባ ፣ መጋቢት 7 ፣ 2013 የአሜሪካ ጦር የሞዛምቢክ ባህር ሃይል የጂሃዲስቶችን አመጽ ለመውጋት ያግዘው ዘንድ ሊያሰለጥን መሆኑ ተነገረ ፡፡ የሞዛምቢክ ባህር ሃይል በሀገሪቱ ሰሜን ምስራቅ ካቦ ዴልጋዶ ግዛት ውስጥ የሚገኘውን የጂሃዲስት አመጽ ለመዋጋት የሚያስችለውን አቅም የአሜሪካ ልዩ ኦፕሬሽን ሃይል ለሁለት ወራት እንደሚያስታጥቀው በማፑቶ የሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ አስታውቋል፡፡ በአካባቢው አል- ሸባብ በመባል የሚታወቁት የታጠቁት […]

ከፍጥነት ወሰን በላይ በማሽከርከር የሚደርሰውን የትራፊክ አደጋ ለመቀነስ የተጠናከረ ቁጥጥር እንደሚያስፈልግ ተጠቆመ::

አዲስ አበባ ፣ መጋቢት 7 ፣ 2013 ከፍጥነት ወሰን በላይ በማሽከርከር የሚደርሰውን የትራፊክ አደጋ ለመቀነስ የተጠናከረ ቁጥጥር እንደሚያስፈልግ ተጠቆመ:: ከፍጥነት ወሰን በላይ በማሽከርከር እየደረሰ ያለውን የትራፊክ አደጋ ለመቀነስ የተጠናከረ ቁጥጥር ማድረግ እንደሚገባ የብሔራዊ መንገድ ደህንነት ፕሮጀክት ጽህፈት ቤት ገለጸ። ለፌደራል እና የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አባላት እንዲሁም ለትራፊክ ማኔጅመንት ጽህፈት ቤት አባላት የአደጋውን ምክንያት ለመቀነስ […]