loading
አንዲት በጎ አድራጊ ግለሰብ ለዘውዲቱ ሆስፒታል ዘመናዊ የአምቡላንስ ድጋፍ አደረጉ፡፡

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 2፣ 2014 አንዲት በጎ አድራጊ ግለሰብ ለዘውዲቱ ሆስፒታል ዘመናዊ የአምቡላንስ ድጋፍ አደረጉ፡፡ የዘውዲቱ ሆስፒታል ፋርማሲስት የሆኑት ወይዘሮ ሃና ልካስ ለሆስፒታሉ ያደረጉት የአምቡላንሶ ድጋፍ በገንዘብ ሲተመን ከ12 ሚሊዮን ብር በላይ የሚያወጣ ሲሆን፥ በተለይ በእርግዝና ላይ ያሉ እናቶች አስፈላጊውን የህክምና ድጋፍ እያገኙ ወደ ሆስፒታል እንዲደርሱ እንደሚያስችል ተገልጿል፡፡ አምቡላንሱ ዘመናዊ የመተንፈሻ ቬንትሌተር የተገጠመለት ሲሆን፤በተለይ እናቶች […]

በደቡብ ሱዳን የኮሌራ በሽታ መከሰቱ በደቡብ ሱዳን በተከሰተው የኮሌራ በሽታ አንድ ሰው ሲሞት 31 ሰዎች በበሽታው መያዛቸው ታውቋል ተባለ፡፡

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 2፣ 2014 በደቡብ ሱዳን የኮሌራ በሽታ መከሰቱ በደቡብ ሱዳን በተከሰተው የኮሌራ በሽታ አንድ ሰው ሲሞት 31 ሰዎች በበሽታው መያዛቸው ታውቋል ተባለ፡፡ የሀገሪቱ የጤና ሚኒስቴር ባወጣው መግለጫ እንደ አውሮፓዊያኑ አቆጣጠር ከ2017 ወዲህ በደቡብ ሱዳን የኮሌራ በሽታ ሲከሰት ይህ የመጀመሪያው ነው ተብሏል፡፡ በሽታው የተከሰተው በሰሜናዊ የሀገሪቱ ክፍል በምትገኘው ዩኒቲ ግዛት ሩቦንካ ካውንቲ ሲሆን በበሽታው […]

በኢትዮጵያ ፍትህ እንዲረጋገጥ ብዙ ስራዎች ይቀራሉ-ኢ.ሰ.መ.ኮ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 3፣ 2014 በየደረጃው ያሉ የመንግሥት አስፈጻሚ አካላትና ኃላፊዎች ለሰብአዊ መብቶች መከበር አስተዋጽኦ እንዲያደርጉ ጥሪ ቀረበ፡፡ ጥሪው የቀረበው የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን የ10 ወር የሥራ  ክንውን ሪፖርቱን ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሕግ፣ የፍትሕ እና የዴሞክራሲ ጉዳዮች  ቋሚ  ኮሚቴ ባቀረበበት ወቅት ነው፡፡ ኮሚሽኑ ባለፉት 10 ወራት ግጭት የተከሰተባቸው 65 ቦታዎችን መድረሱን፣ ባለፉት 3 ወራት ብቻ 450 ሺህ ስደተኞችን የሚያስጠልሉ አስር […]

በጎዳና ላይ የሚኖሩ 9 ሺህ ህጻናትን ወደ ቤተሰቦቻቸው ለመቀላቀል የሚያስችል የአምስት ዓመት ፕሮጀክት ይፋ ሆነ።

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 3፣ 2014 በጎዳና ላይ የሚኖሩ 9 ሺህ ህጻናትን ወደ ቤተሰቦቻቸው ለመቀላቀል የሚያስችል የአምስት ዓመት ፕሮጀክት ይፋ ሆነ። ፕሮጀክቱ በኤስ. ኦ .ኤስ የህጻናት መንደር ኢትዮጵያ የሚመራ ሲሆን ከመንግስት አካላት ጋር በመተባበር በአዲስ አበባ፣ አዳማና ድሬዳዋ ከተሞች የሚተገበር ይሆናል። በኢትዮጵያ ኑሯቸውን በጎዳና ላይ ካደረጉ ከ150 ሺህ በላይ ህጻናት መካከል 60 ሺህ የሚሆኑት በአዲስ አበባ […]

ለቶማስ ሳንካራ ቤሰቦች የተወሰነው 1 ነጥብ 2 ሚሊዮን ዩሮ የካሳ ክፍያ…

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 3፣ 2014 በፕሬዚዳንት ቶማስ ሳናካራ ግድያ የተጠረጠሩት ፕሬዚዳንት ብላሲ ኮምፓዎሬና አጋሮቻቸው 1 ነጥብ 2 ሚሊዮን ዩሮ ካሳ እንዲከፍሉ ተወሰነባቸው፡፡ የቀድሞው ፕሬዚዳንት ብሌስ ኮምፓወሬ ከሌሎች 9 ተከሳሾች ጋር ነው ላደረሱት የሞራልና የኢኮኖሚ ጉዳት ካሳውን እንዲከፍሉ የተወሰነባቸው፡፡ ከኮምፓዎሬ ጋር ፍርድ ከተላለፈባቸው ግለሰቦች መካከል የፕሬዚዳንቱ ጥበቃ ክፍል አዛዥ የነበሩት ሃይሲንቴ ካፋዶ፣ የመከላከያ ኢታማጆር ሹሙ ጊልበርት […]

ኢትዮጵያ በቀይ ባሕር ጉዳይ የቅርብ ተመልካች ሆና እንደማትቀጥል አቶ ደመቀ መኮንን ተናገሩ፡፡

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 9፣ 2014 ኢትዮጵያ በቀይ ባሕር ጉዳይ የቅርብ ተመልካች ሆና እንደማትቀጥል አቶ ደመቀ መኮንን ተናገሩ፡፡ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ አቶ ደመቀ በቀጠናው የወደብ አማራጮችን ለማስፋት በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ አቶ ደመቀ ይህን ያሉት የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴርን የዘጠኝ ወራት የስራ ክንውን ሪፖርት ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባቀረቡበት ወቅት ነው፡፡ በማብራሪያቸው ወቅትም ይህ […]

የማሊ ወታደራዊ መንግስት ለተቃጣበት መፈንቅለ መንግስት ምዕራባዊያንን ወቀሰ፡፡

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 9፣ 2014 የማሊ ወታደራዊ መንግስት ለተቃጣበት መፈንቅለ መንግስት ምዕራባዊያንን ወቀሰ፡፡ ራሱ በመፈንቅለ መንግስ ስልጣን የያዘው የኮሎኔል አሲሚ ጎይታ አስተዳደር የተቃጣበትን መልሶ ግልበጣ የጸጥታ ሃይሎች እንዳከሸፉት ገልጿል፡፡ የአሁኑ የመንግስት ግልበጣ ሙከራ እንደ አውሮፓዊያኑ አቆጣጠር ከ2020 ወዲህ ሁለት መፈንቅለ መንግስት ላስተናገደችው ማሊ ፖለቲካዊ ትኩሳቷ እንዳይበርድ ያደርጋል የሚል ስጋት ፈጥሯል ነውየተባለው፡፡ ወታደራዊ መንግስቱ በመግለጫው ከከሸፈው […]

የዓለም አቀፉ ማህበረሰብ አሸባሪው ህወሃት ለዳግም ጦርነት የሚያደርገውን ዝግጅት እንዲያወግዝ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ጥሪ አቀረበ፡፡

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 10፣ 2014 የዓለም አቀፉ ማህበረሰብ አሸባሪው ህወሃት ለዳግም ጦርነት የሚያደርገውን ዝግጅት እንዲያወግዝ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ጥሪ አቀረበ፡፡ የዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃንና ጋዜጠኞች አሸባሪው ህወሃት በትግራይ ክልል በአስገዳጅ ሁኔታ ነዋሪዎችን ከታዳጊ እስከ አዛውንት ለጦርነት እየመለመለ እንደሆነ በማጋለጥ ላይ ይገኛሉ ብሏል ሚኒስቴሩ። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ […]

አዲሱ የሶማሊያ ፕሬዚዳንት ሀሰን ሸይክ ሞሐመድ በቅርብ ጊዜ የፀጥታ ስራውን ከሰላም አስከባሪ ሃይሉ እንረከባለን አሉ፡፡

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 10፣ 2014 አዲሱ የሶማሊያ ፕሬዚዳንት ሀሰን ሸይክ ሞሐመድ በቅርብ ጊዜ የፀጥታ ስራውን ከሰላም አስከባሪ ሃይሉ እንረከባለን አሉ፡፡በሀገሪቱ የደህንነት ስጋት የሆነውን አልሸባብን ለማጥፋት ቁጥር አንድ መፍትሄ ወታደራዊ ጥንካሬ ነው ያሉት ፕሬዚዳንቱ የአፍሪካ ህብረት የሰላም አስከባሪ ሃይል እስካሁን ላደረገው ድጋፍ ምስጋና አቅርበዋል፡፡ ፕሬዚዳንቱ ከአናዶሉ የዜና ወኪል ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ የሀገራቸው ቀዳሚ ችግሯ የፀጥታ […]

በኢትዮጵያ የዲጂታል ግብይትን ማስፋፋት

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 11፣ 2014 ኢትዮ ቴሌኮም እና ኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳዳር ከሰባት ከተሞች ጋር ስምምነት አደረጉ፡፡ ተቋማቱ ስምምነቱን የፈጸሙት ከክልሎቹ የውሀና ፍሳሽ ባለስልጣኖች ጋር ሲሆን ስምምነቱም የደንበኞችን ክፍያ በቴሌ ብር ማዘመን የሚያስችል ነው፡፡ በስምምነቱ የተካተቱት ከተሞች ሐረሪ፣ ባሕር ዳር፣ ፍኖተሰላም፣ እንጅባራ፣ ደሴና ኮምቦልቻ መሆናቸውን የባልደረባችን ባምላክ ወርቁ ዘገባ ያመለክታል፡፡ በተጠቀሱት ከተሞች የሚገኙ የውሀ አገልግሎት […]