loading
ስድስተኛው ሀገራዊና ክልላዊ ምርጫ በሰላም እንዲጠናቀቅ በትብብር እየሰሩ መሆናቸውን ፓርቲዎች ገለጹ::

አዲስ አበባ፣የካቲት 25፣ 2013 ስድስተኛው ሀገራዊና ክልላዊ ምርጫ በሰላም እንዲጠናቀቅ በትብብር እየሰሩ መሆናቸውን ፓርቲዎች ገለጹ:: በጋምቤላ ክልል የሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፓርቲዎች አመራሮች  ምርጫው ያለንዳች እንከን እንዲሳካ ሰላማዊና ዴሞክራሲዊ ፉክክር  ለማድረግ እየተዘጋጁ መሆናቸውን አመራሮቹ  ተናግረዋል። የብልጽግና ፓርቲ ጋምቤላ ክልል ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ላክድር ላክባክ እንዳሉት ፤ ብልጽግና በክልሉ ከሚገኙት የፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር ካለፈው ዓመት ጀምሮ በትብብር እየሰራ […]

ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ ዩኒቨርሲቲው የማኅበረሰቡን ችግር ለመፍታት የጀመራቸውን ስራዎች እንዲያጠናክር አሳሰቡ::

አዲስ አበባ፣የካቲት 26፣ 2013 ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ ዩኒቨርሲቲው የማኅበረሰቡን ችግር ለመፍታት የጀመራቸውን ስራዎች እንዲያጠናክር አሳሰቡ:: ፕሬዚዳንቷ ይህን ያሉት የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ዩኒቨርሲቲው 70ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን ባከበረበት ወቅት ነው። ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ በቪዲዮ ባስተላለፉት መልዕክት ዩኒቨርሲቲው በአፍሪካ ቀዳሚ እንደመሆኑ ለአፍሪካዊያን ወንድምና እህቶች የትምህርት እድል በመስጠት ያበረከተው አስተዋጽኦ የሚዘነጋ አይደለም ብለዋል። ዩኒቨርሲቲው ቀዳማዊ ኃይለስላሴ ዩኒቨርሲቲ ይባል በነበረበት […]

የሮማው ሊቀጳጳስ አባ ፍራንሲስ በኢራቅ የሚያደርጉት ጉብኝት የበርካቶችን ቀልብ ስቧል::

አዲስ አበባ፣የካቲት 26፣ 2013 የሮማው ሊቀጳጳስ አባ ፍራንሲስ በኢራቅ የሚያደርጉት ጉብኝት የበርካቶችን ቀልብ ስቧል:: ፖፕ ፍራንሲስ በኢራቅ ይፋዊ ጉብኝት ሲያደርጉ የመጀመሪያቸው ሲሆን የኮሮቫይረስ ከተከሰተ ወዲህ ዓለም አቀፍ ጉ ሲያደርጉም ቀዳሚው ነው ተብሏል፡፡ የፖፑ ጉብኝት በኢራቅ ለሚገኙ ክስርስቲያኖች ልዩ ሃይማኖታዊ ትርጉም ያለው ሲሆን በጥንታዊት ባቢሎን ዘመን ጀምሮ የነበረውን የባህልና የቋንቋ እሴቶች ትስስር ያጠናክራል ነው የተባለው፡፡ ሊቀጳጳሱ […]

በዐቢይ ፆም ወቅት ሰላም፣ ፍቅር፣ ይቅር ባይነት መታዘዝና አካፍሎ መብላትን መተግበር እንደሚገባ ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ገለፁ፡፡

አዲስ አበባ፣የካቲት 29፣ 2013 በዐቢይ ፆም ወቅት ሰላም፣ ፍቅር፣ ይቅር ባይነት መታዘዝና አካፍሎ መብላትን መተግበር እንደሚገባ ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ገለፁ፡፡ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ፓትርያርክ ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ በዐቢይ ፆም ወቅት ሰላም፣ ፍቅር፣ ስምምነት፣ ይቅር ባይነት መታዘዝና አካፍሎ መብላትን ምዕመኑ መተግበር እንደሚገባው ጥሪ አቅርበዋል፡፡ ፓትርያርኩ የዐቢይ ጾም መግባትን ምክንያት በማድረግ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡ በመግለጫቸውም […]

ለሴቶች ከፍ ያለ ደረጃ መድረስ ከትምህርት ሌላ ምንም መሰላል እንደሌለ ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ ገለጹ ፡፡

አዲስ አበባ፣የካቲት 29፣ 2013 ለሴቶች ከፍ ያለ ደረጃ መድረስ ከትምህርት ሌላ ምንም መሰላል እንደሌለ ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ ገለጹ ፡፡ ሴቶች በትምህርታቸው ውጤታማ በመሆን ከፍተኛ የሃላፊነት ቦታዎችን በብቃት መምራት እንደሚችሉ አምነው እንዲማሩ ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ መክረዋል።ፕሬዚዳንቷ  ዓለም አቀፉን የሴቶች ቀን ምክንያት በማድረግ የቱሉ ዲምቱ ሁለተኛና መሰናዶ ትምህርት ቤትን ጎብኝተዋል። በጉብኝታቸው ከትምህርት ቤቱ የስርዓተ ጾታ ክበብ አባላት ጋር […]

በህዳሴው ግድብ ግንባታና የውሃ አሞላል ሂደት ዙሪያ በትብብር ለመስራት ያሉ ፈተናዎችና መልካም አጋጣሚዎች ላይ ያተኮረ ውይይት ተካሄደ ፡፡

አዲስ አበባ፣የካቲት 29፣ 2013 በህዳሴው ግድብ ግንባታና የውሃ አሞላል ሂደት ዙሪያ በትብብር ለመስራት ያሉ ፈተናዎችና መልካም አጋጣሚዎች ላይ ያተኮረ ውይይት ተካሄደ ፡፡ የውይይቱ ዓላማ በግድቡ ዙሪያ በእውነታ ላይ የተመሰረተና ትክክለኛ መረጃን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ማስተላለፍ ነው ተብሏል፡፡ ውይይቱ በዌብናር የተካሄ ሲሆን በውይይተቱ ከተሳተፉት መካከል በሀገር ውስጥና በአሜሪካን ሀገር የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን እንዲሁም አሜሪካዊያን ይገኙበታል፡፡ ተወያዮቹ በዋናነት […]

በኢኳቶሪያል ጊኒ በአንድ ወታደራዊ ካምፕ በደረሰ ፍንዳታ 20 ሰዎች ሲሞቱ በርካታ ሰዎች ቆስለዋል፡፡

አዲስ አበባ፣የካቲት 29፣ 2013 በኢኳቶሪያል ጊኒ በአንድ ወታደራዊ ካምፕ በደረሰ ፍንዳታ 20 ሰዎች ሲሞቱ በርካታ ሰዎች ቆስለዋል፡፡ በወታደራዊ ካምፑ ላይ አራት ከፍተኛ ፍንዳታዎች መድረሳቸው የታወቀ ሲሆን ከሞቱት 20 ሰዎች በተጨማሪ 600 የሚሆኑት ደግሞ መቁሰላቸው ተሰምቷል፡፡ ፍንዳታው የደረሰው የኢኮኖሚ ከተማ በሆነችው ባታ ከተማ አቅራቢያ በሚገኘው ንኮማ ንቶማ ወታደራዊ ካምፕ ነው፡፡ የፍንዳታው መንስኤ በአካባቢው የሚገኙ አርሶ አደሮች […]

በአሜሪካ በኮቪድ-19 ሳቢያ የሚሞቱ ሰዎች ቁጥር ከወራት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ መቀነሱ ተሰማ፡፡

አዲስ አበባ፣የካቲት 30፣ 2013 በአሜሪካ በኮቪድ-19 ሳቢያ የሚሞቱ ሰዎች ቁጥር ከወራት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ መቀነሱ ተሰማ፡፡ ከሶስት ወር ተኩል በኋላ በአሜሪካ በየቀኑ የሚሞቱት ሰዎች ቁጥር ከ1 ሺህ በታች ሆኖ መመዝገቡን ጆን ሆፕኪንስ ዩኒቨርሲቲ ይፋ አድርጓል፡፡ ለአሜሪካዊያን በ24 ሰዓታት ውስጥ በቫይረሱ የሞቱ ሰዎች 749 ብቻ መሆናቸው ከወራት በኋላ የተሰማ መልካም ዜና ሆኗል፡፡ ፍራንስ 24 እንደዘገበው 10 […]

የኒጄሩ ፕሬዚዳንት ማማዱ ኢሱፎ የ2020 የሞ ኢባራሂም ሽልማት አሸነፉ::

አዲስ አበባ፣የካቲት 30፣ 2013 የኒጄሩ ፕሬዚዳንት ማማዱ ኢሱፎ የ2020 የሞ ኢባራሂም ሽልማት አሸነፉ:: ኢሱፉ ሽልማቱን ያገኙት በሀገራቸው የተከሰቱ በርካታ ችግሮች በቁርጠኝነት በመጋፈጥ ለህዝባቸው ጠቃሚ ስራ ሰርተዋል በሚል ነው፡፡ በተለይ በኒጄር ነፍጥ አንግበው ሽብር የሚፈጥሩ ሀይሎችን በመዋጋት፣ በርሃማነትን በመከላከል የልማት ስራዎችን በመስራት ረገድ አመርቂ ውጤት አስገኝተዋል ነው የተባለው፡፡ ፕሬዚዳንት ኢሱፉ ሀገራቸውን ለ10 ዓመት ካገለገሉ በኋላ ስልጣናቸውን […]

በሀገራችን ያለውን የአይን ህክምና ዘርፍ ከፍ የሚያረግ እና የተሻለ ህክምና የሚገኝበት ላቪስታ የአይን ህክምና ክሊኒክ ተመርቆ ስራ ጀመረ::

አዲስ አበባ ፣ መጋቢት 6 ፣ 2013 በሀገራችን ያለውን የአይን ህክምና ዘርፍ ከፍ የሚያረግ እና የተሻለ ህክምና የሚገኝበት ላቪስታ የአይን ህክምና ክሊኒክ ተመርቆ ስራ ጀመረ:: ላቪስታ የአይን ህክምና በሀገራችን ያለውን የአይን ህክምና ዘርፍ ለማገዝና በተሻለ ለመስራት መቋቋሙ ተነግሯል፡፡ እንዲሁም በአዳዲስ የአይን ህክምና መሳሪያዎች በመታገዝ ታካሚዎች የተሻሉ የተባሉ መሳሪያዎች ለማግኘት ወደ ውጪ ሀገር ሄደው ለመታከም የሚገደዱበትን […]