loading
የመካነ ቅርሶች ጉብኝት በኢትዮጵያ ቅርስና ጥበቃ ባለስልጣን መስሪያ ቤት አስተባባሪነት እየተደረገ መሆኑ ተገለፀ።

አዲስ አበባ፣የካቲት 5፣ 2013 የመካነ ቅርሶች ጉብኝት በኢትዮጵያ ቅርስና ጥበቃ ባለስልጣን መስሪያ ቤት አስተባባሪነት እየተደረገ መሆኑ ተገለፀ።የኢትዮጵያ ቅርስና ጥበቃ ባለስልጣን መስሪያ ቤት በደቡብ እና ምእራብ የኢትዮጵያ ክፍሎች ለመገናኛ ብዙሀን ያዘጋጀው ለሳምንት የሚዘልቅ ጉብኝት በመካሄድ ላይ ይገኛል። በጉብኝቱ የቅርስና ጥበቃ ባለሙያዎች ፣ የጥናት ባለሙያዎች እንዲሁም የመገናኛ ብዙሀን ሙያተኞች እየተሳተፉ ይገኛል። ይህ የኢትዮጵያን የአገር ውስጥ ቱሪዝም ለማበረታት […]

አዲስ አበባ እና ድሬዳዋን ጨምሮ በአራት ክልሎች የዕጩዎች ምዝገባ ዛሬ ይጀመራል::

አዲስ አበባ፣የካቲት 8፣ 2013 አዲስ አበባ እና ድሬዳዋን ጨምሮ በአራት ክልሎች የዕጩዎች ምዝገባ ዛሬ ይጀመራል:: አዲስ አበባ እና ድሬዳዋ ከተማ አስተዳደርን ጨምሮ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ፣ ጋምቤላ፣ ኦሮሚያ እና ሐረሪ ክልሎች የዕጩዎች ምዝገባ ዛሬ ይጀመራል። ምዝገባው የሚከናወነው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለዕጩዎች ምዝገባ ባወጣው ከየካቲት 08 እስከ የካቲት 21 ቀን 2013 ዓ.ም የጊዜ ሰሌዳ መሠረት ነው። የምርጫ […]

ዩናይትድ አርብ ኤሚሬት በእስራኤል የሚያገለግላትን አምባሳደር ሰየመች፡፡

አዲስ አበባ፣የካቲት 8፣ 2013 ዩናይትድ አርብ ኤሚሬት በእስራኤል የሚያገለግላትን አምባሳደር ሰየመች፡፡ መሃመድ አል ካጃ በእስራኤል የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች አምባሳደር ሆነው ተሾመዋል፡፡ መሃመድ አል ካጃ በሀገሪቱ ምክትል ፕሬዝዳንት ፣ ጠ/ሚኒስትር እና የዱባይ ገዥ ሼክ መሀመድ ቢን ራ ሺድ ፊት እሁድ ዕለት በአቡ ዳቢ የአል-ዋታን ቤተመንግስት ቃለ መሃላ ፈጽመዋል፡፡ ሚስተር አል ካጃ የተባበሩት አረብ ኤሚሬቶችን ሕገ- መንግስት እና ሌሎች ህጎች በማክበር ለብሔራዊ ጥቅሟ መከበር ቅድሚያ ሰጥተው እንደሚሰሩ ቃል […]

በዋግኽምራ ዞን 150 ሚሊየን ብር ወጪ የተገነባው የንጹህ መጠጥ ውኃ ፕሮጀክት ተመረቀ፡፡

አዲስ አበባ፣የካቲት 8፣ 2013 በዋግኽምራ ዞን 150 ሚሊየን ብር ወጪ የተገነባው የንጹህ መጠጥ ውኃ ፕሮጀክት ተመረቀ፡፡ በዋግኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ድሃና ወረዳ 150 ሚሊየን ብር ወጪ የተገነባው የንጹህ መጠጥ ውኃ ፕሮጀክት ተመርቋል። በምርቃቱ ላይ የአማራ ክልል ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ወይዘሮ ወርቅሰም ማሞና የአማራ ክልል ምክትል ርእሰ መሥተዳድር ዶክተር ፋንታ ማንደፍሮን ጨምሮ የክልልና የብሔረሰብ አስተዳደሩ ከፍተኛ […]

ጊኒ የኢቦላ ቫይረስ በወረርሽኝ ደረጃ መከሰቱን ይፋ አደረገች።

አዲስ አበባ፣የካቲት 8፣ 2013 ጊኒ የኢቦላ ቫይረስ በወረርሽኝ ደረጃ መከሰቱን ይፋ አደረገች። በጊኒ ደቡብ ምስራቅ በተከሰተው የኢቦላ ወረርሽኝ ለህልፈት ከተዳረጉት ሰዎች ባሻገር አራት ሰዎች ደግሞ ቫይረሱ እንደተገኘባቸው ተነግሯል። በደቡብ ምስራቅ የሀገሪቱ ክፍል በምትገኘው ጎዋኬ በአንድ የቀብር ስነ ስርዓት ላይ የተሳተፉ 7 ሰዎች የማስመለስ፣ የመድማት እና ማስቀመጥ  እንዳጋጠማቸው ተጠቁሟል። የኢቦላ ቫይረስ የተገኘባቸው እነዚህ ሰዎች አሁን ላይ […]

የዓለም ጤና ድርጅት አዲሱ የኮሮናቫይረስ ዝርያ ባለፈው ሳምንት በ16 በመቶ ቀንሶ መታየቱን ገለፀ፡፡

አዲስ አበባ፣የካቲት 10፣ 2013 የዓለም ጤና ድርጅት አዲሱ የኮሮናቫይረስ ዝርያ ባለፈው ሳምንት በ16 በመቶ ቀንሶ መታየቱን ገለፀ፡፡ ድርጅቱ ማክሰኞ አመሻሽ ላይ ባወጣው ሪፖርት ከኮቪድ 19 ጋር የተያያዘ የሞት መጠን መቀነሱንም አስታውሷል፡፡ ድርጅቱ ከስድስት የቁጥጥር ቀጠናዎች ከተላኩለት የበሽታው ስርጭት ሪፖርቶች መካከል በአምስቱ አዲሱ ቫይረስ በሁለት አሃዝ መቀነስ ሲያሳይ በሜዲትራኒያን አካባቢ ብቻ በ7 በመቶ ጭማሪ መመዝገቡ ታውቋል፡፡ […]

ኢዜማ መንግስት የፓረቲያቸዉን አባል ሕይወት የቀጠፉትን ወንጀለኞች አድኖ ሕግ ፉት ባስቸኳይ እንዲያቀርብ ጠየቀ፡፡

አዲስ አበባ፣የካቲት 10፣ 2013 ኢዜማ መንግስት የፓረቲያቸዉን አባል ሕይወት የቀጠፉትን ወንጀለኞች አድኖ ሕግ ፉት ባስቸኳይ እንዲያቀርብ ጠየቀ፡፡ የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ ኢዜማ የፓርቲዉ አባል አቶ ግርማ ግድያን ተከትሎ በሰጠዉ መግለጫ ፤ ከዚህ በፊት በቢሾፍቱ ከተማ የምናደርገዉ እንቅስቃሴ ላይ የተለያዩ ችግሮች ሲያጋጥሙ እና አባላቶቻችን ላይ ማዋከብ ሲያገጥመን የቆየ ነዉ ብሏል፡፡ የምርጫ ወረዳ መዋቅራችን የሚጠቀምበት ጽ/ቤት ለመክፍት […]

አልጄሪያዊያን የሂራክ አመፅ ንቅናቄ ብለው የሚጠሩትን የተቃውሞ ሰልፍ ለመዘከር አደባባይ ወጥተዋል፡፡

አዲስ አበባ፣የካቲት 10፣ 2013 አልጄሪያዊያን የሂራክ አመፅ ንቅናቄ ብለው የሚጠሩትን የተቃውሞ ሰልፍ ለመዘከር አደባባይ ወጥተዋል፡፡ የሂራክ ንቅናቄ እንደ አውሮፓዊያኑ አቆጣር በ2019 ፕሬዚዳንት አብደልአዚዝ ቡተፍሊካን ከስልጣን ያስወገዱበት የተቃውሞ ሰልፍ ነው፡፡ ሰልፈኞቹ የኮሮናቫይረስ ሳያስፈራቸውና በአደባባይ በሰባሰብን የሚከለክለውን ህግ ወደጎን በመተው ነው እለቱን እያሰቡ ሌላ ጥያቄ ያነሱበት፡፡ አልጄሪያዊያኑ ያኔ ባነሱት ተቃውሞ ለሁለት አስርት ዓመታት ሀገሪቱን የመሩት ቡተፍላካ ከስልጣን […]

በአፍሪካ በኮቪድ-19 የሞቱ ሰዎች ቁጥር ከ100 ሺህ በላይ መድረሱ ተነገረ፡፡

አዲስ አበባ፣የካቲት 12፣ 2013 በአፍሪካ በኮቪድ-19 የሞቱ ሰዎች ቁጥር ከ100 ሺህ በላይ መድረሱ ተነገረ፡፡ በአህጉሩ የተመዘገበው የሟችና የታማሚዎች ቁጥር ከቀሪው ዓለም ጋር ሲነፃፀር አናሳ ቢሆንም የበሽታው ስርጭት ከነበረበት በፍጥነት እየጨመረ ነው ተብሏል፡፡ በተለይ በአፍሪካ ሁለተኛው ዙር የወረርሽኝ መስፋፋት መከሰቱን ተከትሎ ሆስፒታሎች በሽተኞችን መቀበል እስኪያቅታቸው መጨናነቃቸው ነው የሚነገረው፡፡ አልጀዚራ እንደዘገበው በአፍሪካ በሽታው ከታየ ጀምሮ እስካሁን ድረስ […]

የአልጄሪያው ፕሬዚዳንት አብደልመጅድ ቲቦኒ የሀገሪቱን ፓርላማ በትነው አዲስ ምርጫ እንዲካሄድ ጥሪ አቀረቡ፡፡

አዲስ አበባ፣የካቲት 12፣ 2013 የአልጄሪያው ፕሬዚዳንት አብደልመጅድ ቲቦኒ የሀገሪቱን ፓርላማ በትነው አዲስ ምርጫ እንዲካሄድ ጥሪ አቀረቡ፡፡ ፕሬዚዳንቱ ይህን ውሳኔያቸውን ያሳወቁት አልጄሪያ የሰማእታት ቀንን በምታከብርበት ወቅት ነው ተብሏል፡፡ ቲቦኒ እዚህ ውሳኔ ላይ የደረሱት የተለያዩ የፓርቲ መሪዎች ጋር ተደጋጋሚ ስብሰባዎችና ምክክሮችን ካደረጉ በኋላ መሆኑ ነው የተሰማው፡፡ አፍሪካ ኒውስ እንደዘገበው ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ፕሬዚዳንቱና የካቢኔ አባሎቻቸው ስልጣናቸውን እንዲለቁ […]