loading
የቤተክርስቲያኗን የአደባባይ በዓላት በአለማዊ ክንዋኔዎች እንዳይበረዙ መጠበቅ ያስፈልጋል ተባለ::

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 4 ፣ 2013 የቤተክርስቲያኗን የአደባባይ በዓላት በአለማዊ ክንዋኔዎች እንዳይበረዙ መጠበቅ ያስፈልጋል ተባለ::የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ጠቅላይ ቤተ ክህነት ፅህፈት ቤት የሰበካ ጉባኤ የአደባባይ በዓላት ስኬቶችና ተግዳሮቶች በሚል ባዘጋጀው የፓናል ውይይት ላይ የቤተክርስቲያኗን የአደባባይ በዓላት የበዓላቱን አከባበር ዝግጅት የሚያስተባብር ቋሚ አደረጃጀት ሊኖር ይገባል ብሏል፡፡ በጉዳዩ ላይ መነሻ ፅሁፍ ያቀረቡት መምህር ማለዳ ዘሪሁን […]

ከህግ ያፈነገጠው የአማኑኤል ወንድሙ ግድያ::

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 4 ፣ 2013   የኢትዮጵያ ሰብዐዊ መብቶች ኮሚሽን በኦሮሚያ ክልል ደንቢ ዶሎ ቄለም ወለጋ ዞን በግንቦት 3 2013 ዓም በ ፀጥታ ሀይሎች በአደባባይ ላይ የተገደለው አማኑኤል ወንድሙ ሞት እጅግ ጭካኔ የተሞላበት እና ከህግ ያፈነገጠ ነው ሲል ገልጸ፡፡ ኮሚሽኑ ሁሉንም አይነት ህገ ወጥነት የሞላባቸው ግድያዎችን እንደሚቃወም የገለፀ ሲሆን ሰላም አስከባሪ ሀይላት ሰላም በማስከበሩ […]

በአብዬ በሰላም ማስከበር ግዳጅ ላይ ለተሰማሩ የመከላከያ ሰራዊት አባላት የመጀመሪያ ዙር የኮቪድ- 19 ክትባት ተሰጣቸው፡፡

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 6 ፣ 2013  በአብዬ በሰላም ማስከበር ግዳጅ ላይ ለተሰማሩ የመከላከያ ሰራዊት አባላት የመጀመሪያ ዙር የኮቪድ- 19 ክትባት ተሰጣቸው፡፡ በሱዳን አብዬ ግዛት የሚገኙት የ25ኛ ሞተራይዝድ ሰላም አስለባሪ ሻለቃ አባላት አስትራዜኒካ የተባለው የመጀመሪያ ዙር የኮቪድ 19 መከላከያ ክትባት ነው የተሰጣቸው፡፡ የሻለቃው የህክምና ሃላፊ ሻለቃ ፀሃይ በላቸው ሰራዊቱ እራሱን ከኮቪድ-19 ወረርሽኝ በመከላከል የተሰጠውን አገራዊና […]

ማኅበረሰቡ የኮሮናቫይረስ የመከላከያ መንገዶችን እንዲተገብር የኢትዮጵያ የኅብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት አሳሳበ፡፡

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 6 ፣ 2013 ማኅበረሰቡ የኮሮናቫይረስ የመከላከያ መንገዶችን እንዲተገብር የኢትዮጵያ የኅብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት አሳሳበ፡፡ ኢንስቲትዩቱ በህንድ የተከሰተው አዲስ የኮሮናቫይረስ ዝርያ አሳሳቢ እየኾነ መምጣቱን በማስታወስ ማህበረሰቡ እንዳይዘናጋ አስጠንቅቋል፡፡ የዓለም ጤና ድርጅት በህንድ የተከሰተው የኮሮናቫይረስ ዝርያ ዓለም አቀፍ ስጋት እየሆነ እንደመጣ መግለጹን ኢኒስቲትዩቱ አስታውቋል፡፡ ቫይረሱ እስካሁን በ44 ሀገራት እንደተሰራጨ መገለጹን በማኅበራዊ ትስስር ገጹ አመላክቷል፡፡ […]

በሱዳን በኩል ወደ ሀገር ሊገባ ሲል የተደመሰሰው የህወሃት ቡድን

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 6 ፣ 2013 ከሱዳን በመነሳት በማይካድራ አድርገው ወደ ሀገር ሊገቡ የነበሩ 320 የህወሃት ሀይል አባላት ተደመሰሱ፡፡ የህብረት ዘመቻ ዋና መምሪያ ሀላፊ ተወካይ ብርጋዴር ጄኔራል ተስፋዬ አያሌው እንዳሉት ይህ ቡድን በማይካድራ ጭፍጨፋ አድርሶ ወደ ሱዳን ሸሽቶ የነበረ ነው፡፡ ብርጋዴር ጄኔራል ተስፋዬ በሰጡት መግለጫ ቡድኑ ዳግም ተደራጅቶ የተለያዩ የመገናኛ መሳሪያዎችንና መድሀኒቶችን በመያዝ ወደ […]

በኢትዮጵያ ባለፉት 24 ሰዓታት 20 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ ህይወታቸዉ አለፈ፡፡

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 9 ፣ 2013 በኢትዮጵያ ባለፉት 24 ሰዓታት 20 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ ህይወታቸዉ አለፈ፡፡ የጤና ሚኒስቴር ባለፉት 24 ሰአታት የኮቪድ 19 ስርጭት መረጃ ባሳወቀበት ወቅት እንደገለጸዉ፤ ባለፈት 24 ሰኣታት ዉስጥ 20 ሰዎች በኮቪድ 19 ህወታቸዉን አጥተዋል፡፡ የህም ባጠቃላይ በኮሮና ቫይረስ ህይወታቸዉን ያጡ ሰዎችን ቁጥር 3 ሺህ 9 መቶ 96 ደርሷል፡፡ ባለፉት 24 […]

ቴክኖ ታዋቂውን የሆሊውድ ተዋናኝ ክሪስ ኢቫንስን የቴክኖ አለም አቀፍ የንግድ አምባሳደሩ አድርጎ ሾመው::

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 9 ፣ 2013 ቴክኖ ታዋቂውን የሆሊውድ ተዋናኝ ክሪስ ኢቫንስን የቴክኖ አለም አቀፍ የንግድ አምባሳደሩ አድርጎ ሾመው:: ክሪስ ኢቫንስ በግንቦት 20 በሚደረገው የTECNO የምርት አውደ ርዕይ ላይ የቴክኖ የንግድ አምባሳደር በመሆን የሚቀርብ ሲሆን በሚቀጥሉት የቴክኖ ዓለም አቀፍ የምርት ዘመቻዎች ላይም ቴክኖን በወከል ይሳተፋል:: ዓለም አቀፉ ፕሪሚየም ስማርት ስልክ ብራንድ TECNO ዛሬ ከሆሊሁዱ […]

ኢትዮጵያ በዘርፈ ብዙ ችግሮች ውስጥ ብትሆንም ወደፊት ብሩህ ተስፋ እንደሚጠብቃት የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ተናገሩ፡፡

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 10 ፣ 2013 ኢትዮጵያ በዘርፈ ብዙ ችግሮች ውስጥ ብትሆንም ወደፊት ብሩህ ተስፋ እንደሚጠብቃት የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ተናገሩ፡፡ ተማሪዎቹ ይህን ያሉት የከፍተኛ ትምህርት እና ሳይንስ ሚኒቴር፣ ከፒፕል ቱ ፒፕል፣ ከአፍሪኮም ሲምፖዚየምና ከኢንተርናሽናል ኔትወርክ ፎር ሀየር ኢጁኬሽን ኢን አፍሪካ ጋር ባዘጋጀው የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ውይይትና ክርክር መድረክ ላይ ነው፡፡ ውይይቱ በዋናነት ያተኮረው ታላቁ የህዳሴው ግድብና […]

ኢትዮጵያዊያን የኢትዮጵያ ሳምንት ፌስቲቫልን እንዲጎበኙ ጥሪ ቀረበ።

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 10 ፣ 2013 ኢትዮጵያዊያን የኢትዮጵያ ሳምንት ፌስቲቫልን እንዲጎበኙ ጥሪ ቀረበ።የባህል እና ቱሪዝም ሚኒስትር ዶ/ር ሂሩት ካሣው፣ የከተማ ልማት እና ኮንስትራክሽን ሚኒስትር ኢንጂነር አይሻ መሐመድ እና የሴቶች፣ ወጣቶች እና ሕፃናት ሚኒስትር ፊልሰን አብዱላሂ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድን ጨምሮ ከፍተኛ የስራ ሀላፌዎች በተገኙበት የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።

የኢትዮጵያ ሳምንት በወዳጅነት ፓርክ እየተካሄደ ነው።

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 10 ፣ 2013 የኢትዮጵያ ሳምንት በወዳጅነት ፓርክ እየተካሄደ ነው። በ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሀሳብ አመንጪነት በ 3 ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶች የተዘጋጀው ፌስቲቲቫሉ ሀገሪቱ ያላትን ሀብትና የተፈጥሮ ፀጋ ለማስተዋወቅ እንዲሁም ወደ ኢንቨስትመንት አማራጭ ለመለወጥ ያለመ ነው። በፌስቲቫሉ ላይ የተለያዩ ክልሎች ልዩ መገለጫችን ያሉትን ባህላቸውን እያስተዋወቁበት ይገኛሉ። መሰል ፌስቲቫሎች ከሀገሪቱ ወቅታዊ ሁኔታ አንፃር መዘጋጀታቸው […]