loading
ምርጫው ከነችግሮቹም ቢሆን የተሻለ ሂደት ታይቶበታል-ኢሰመጉ::

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 25፣ 2013  6ኛው ሀገራዊ ምርጫ ለዴሞክራሲ ባህል ግንባታ መሠረት የጣለና በአንፃራዊነት ስኬታማ እንደነበረ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ጉባኤ አስታወቀ። ኢሰመጉ በቅድመ ምርጫ፣ በድምፅ መስጫ ዕለትና ድህረ ምርጫ ወቅቶች ያለውን አጠቃላይ ሂደት አስመልክቶ መግለጫ ሰጥቷል። ምርጫው በተከናወነባቸው በአብዛኞቹ የሀገሪቱ አካባቢዎች የጎላ የጸጥታ ችግር አለማጋጠሙን የገለጸው ተቋሙ የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ ለሚፈጠሩ ችግሮች ምላሽ የሰጠበትን […]

የቻይና መንግስት ህገ ወጥ አዘዋዋሪ ነው- አንቶኒ ብሊንከን

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 25፣ 2013 አሜሪካ ቻይናና ሩሲያን ጨምሮ ከ10 በላይ ሀገሮችን በህገ ወጥ ሰዎች ዝውውርና በግዳጅ የጉልበት ብዝበዛ ከሰሰች፡፡ የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን በሰጡት መግለጫ ከሩሲያና ቻይና በተጨማሪ ማይናማር እና ቱርክ በዚሁ ተግባር ይሳተፋሉ የሚል ወቀሳ አቅርበዋል፡፡ ብሊንከን በተለይ ሺንጂያንግ ግዛት አካሂዶታል ያሉትን የጅምላ እስር እና ተያያዥ ተግባራትን በመጥቀሽ የቻይና መንግስት […]

የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት 6ኛ ዓመት የስራ ዘመን 4ኛ ልዩ ስብሰባውን እያካሄደ ነው::

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 28፣ 2013 ምክር ቤቱ ልዩ ስብሰባውን የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በተገኙበት ነው እያካሄደ የሚገኘው፡፡ ምክር ቤቱ በልዩ ስብሰባው የፌዴራል መንግስትን የ2014 በጀት ዓመት ረቂቅ በጀት ላይ ተወያይቶ እንደሚያፀድቅ ይጠበቃል፡፡ በምክር ቤቱ ስብሰባ መክፈቻ ላይ የሃገር መከላከያ ሰራዊት ላበረከተው አስተዋፅኦ የምክር ቤቱ አባላት አድናቆታቸውን በጭብጨባ ገልፀዋል፡፡ በጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት መሰብሰቢያ […]

የሰኔ ወር ዋጋ ግሽበት 24 ነጥብ 5 በመቶ ጭማሪ አሳየ::

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 28፣ 2013 የማዕከላዊ ስታቲስቲክስ ኤጀንሲ በየወሩ የሚያወጣው የዋጋ ግሽበት መረጃ ሁኔታ የሰኔ ወር 2013 ዓ.ም ካለው ጋር ሲነጻጸር በ24 ነጥብ 5 ከመቶ ጭማሬ ማሳየቱ ተገልጿል፡፡ የሰኔ ወር 2013 ዓ.ም የምግብ ዋጋ ግሽበት ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር በ28 ነጥብ 7 በመቶ ጭማሪ አሳይቷል፡፡ በዳቦና እህሎች ላይ የታየው የዋጋ ጭማሪ በያዝነው […]

በኢትዮጵያ ላይ የተደቀነውን ብሔራዊ የደኅንነት ስጋት ለመመከት የሚጠበቅበትን ሁሉ ለማድረግ ቁርጠኛ መሆኑን አብን ገለፀ፡፡

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 28፣ 2013 በኢትዮጵያ ላይ የተደቀነውን ብሔራዊ የደኅንነት ስጋት ለመመከት የሚጠበቅበትን ሁሉ ለማድረግ ቁርጠኛ መሆኑን አብን ገለፀ፡፡ የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) ሥራ አስፈጻሚ ተወያይቶ  የደረሰባቸውን አቋሞች በተመለከተ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል፡፡ አብን በመግለጫው የመራጩ ድምፅ እንዲከበር ሰላማዊና ሕጋዊ ጥረት እንደሚያደርግና የሕዝቡን ሐቀኛ ውሳኔ ያለማወላወል እንደሚቀበል አሳውቋል፡፡ በምርጫው የመሳተፉን ውሳኔ ያደረገው በዋነኝነት ከድርጅታዊ ፋይዳዎች ይልቅ ለሀገራዊ ፖለቲካው መረጋጋትና ለዴሞክራሲያዊ ተሞክሮ ግንባታ ከሚኖረው ፋይዳ አንፃር እንደሆነም ገልጿል፡፡ የምርጫው ሂደት አጠቃላይ ድርጅታዊ ቁመናውን የሚፈትሽበት መልካም አጋጣሚ መሆኑን እንደሚገነዘብ ነው በመግለጫው ያመላከተው፡፡ በቀጣይም ከሂደቱ ያገኛቸውን ተሞክሮዎችና ትምህርቶች በማካተትና ሁለገብ የማሻሻያ እርምጃዎች በመውሰድ ለብሔራዊ ፖለቲካ የሚጠበቅበትን እንደሚወጣ ገልጿል፡፡ የውጭ ወራሪዎችና የውስጥ ቦርቧሪዎች ከተቻለ ኢትዮጵያን ለየዘውጉ አምበሎች በታትኖ ከዓለም ካርታ ለማጥፋት፤ ካልሆነ ደግሞ ውስጣዊ አንድነት የሌላት፣ ደካማና ፍላጎታቸውን ያለማንገራገር የምትቀበል አድርገው ለማሽመድመድ እየተረባረቡ ይገኛሉ ብሏል። በኢትዮጵያ ላይ የተደቀነውን የብሔራዊ የደኅንነት ስጋት ለመመከት የሚጠበቅበትን ሁሉ ለማድረግ ቁርጠኛ መሆኑንም አብን ገልጿል፡፡ ማዕከላዊ መንግሥትና በየደረጃው ያሉ መንግሥታዊ አካላት ሀገሪቱን ከተደቀነባት የህልውና አደጋ ለመታደግ በሚደረገው ርብርብ የራሳቸውን ሚና በግልጽ ከመወሰን አንስቶ ሁሉንም ባለድርሻ አካላት ያካተተ የብሔራዊ ደኅንነት እርምጃ እንዲወስዱም አብን ጥሪ አቅርቧል፡፡ መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ፣ ሀገር ወዳድ ዜጎችና በተለይም ወጣቱ የኅብረተሰብ ክፍል ሀገሪቱ ስለገጠማት የብሔራዊ የደኅንነት አደጋ ግልጽ ግንዛቤ እንዲኖራቸውና ኢትዮጵያን ለመታደግ በአንድነት እንዲሰለፉም ጠይቋል፡፡ በትግራይ ክልል በሚገኙ ዩኒቨርስቲዎች ተመድበው ትምህርታቸውን በመከታተል ላይ የሚገኙ ተማሪዎችን የትግራይ ሕዝብ አስፈላጊውን ጥበቃና እክብካቤ እንዲያደርግ ጥሪውን አስተላልፏል፡፡

የትምህርት ሚኒስቴር የአቅመ ደካሞችን ቤት በማደስ የክረምት በጎ አድራጎት መርሀ-ግብር በይፋ ተጀመረ::

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 29፣ 2013 የትምህርት ሚኒስቴር የአቅመ ደካሞችን ቤት በማደስ የክረምት በጎ አድራጎት መርሀ-ግብር በይፋ ተጀመረ:: የሚኒስቴሩ ከፍተኛ አመራሮች በአራዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ 9 የአቅመ ደካሞችን ቤቶች በማደስ በትምህርት ዘርፉ የሚካሄደውን የክረምት የበጎ አድራጎት መርሀ-ግብርን በይፋ አስጀምረዋል። በበጎ አድራጎት መርሀ ግብሩም በትምህርት ሚኒስቴር ድጋፍ በክፍለ ከተማው 15 የአቅመ ደካሞች ቤት እንደሚታደስም ተገልጿል። የትምህርት […]

ካይሮ የግድቡ ሁለተኛው ዙር የውሃ ሙሌት መጀመሩን የሚገልፅ ደብዳቤ ከአዲስ አበባ ደርሶኛል አለች፡፡

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 29፣ 2013 ካይሮ የግድቡ ሁለተኛው ዙር የውሃ ሙሌት መጀመሩን የሚገልፅ ደብዳቤ ከአዲስ አበባ ደርሶኛል አለች፡፡ የግብፅ የመስኖ ሚኒስትር ሞሀመድ አብደል አቲ የኢትዮጵያው የውሃ፣ መስኖና ኢነርጅ ሚኒስትር ኢንጂኔር ስለሺ በቀለ በላኩልኝ ይፋዊ ደብዳቤ ሀገራቸው በተናጠል ውሳኔዋ ፀንታ ሁለተኛውን ዙር ሙሌት መጀመሯን አረጋግጠውልኛል ብለዋል፡፡ አብደል አቲ ለኢንጂኔር ስለሺ በጻፉት የመልስ ደብዳቤ ግብፅ የኢትዮጵያን […]

የክብርት ዶክተር አበበች ጎበና የቀብር ስነ-ስርዓት በቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ተፈጸመ፡፡

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 29፣ 2013 በቀብር ስነ ስርዓቱ ላይ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስትያን ፓትርያሪክ ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ማቲያስ፣ የጤና ሚኒስትሯ ዶክተር ሊያ ታደሰ፣ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳና የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ ተገኝተዋል፡፡ አፍሪካዊቷ ማዘር ቴሬዛ በመባል የሚታወቁት ክብርት ዶክተር አበበች ጎበና ከሀገር ባለውለታነት አልፈው ለሰው ልጆች ትልቅ […]

የፀጥታው ምክር ቤት በህዳሴው ግድብ ውሳኔ የመስጠት ኃላፊነት የለውም-የናይል ተፋሰስ ሀገራት

አዲስ አበባ ፣ ሃምሌ 1፣ 2013  የፀጥታው ምክር ቤት በህዳሴው ግድብ ውሳኔ የመስጠት ኃላፊነት የለውም-የናይል ተፋሰስ ሀገራት የናይል ተፋሰስ ሀገራት በአፍሪካ ህብረት አስተባባሪነት የሚደረገው የግድቡ ድርድር ሂደት ሰላማዊ መፍትሄ ለማምጣት ትክከለኛው መንገድ መሆኑን ገለጹ፡፡ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና ውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ አቶ ደመቀ መኮንን ድርድሩ ያለበትን ደረጃ በሚመለከት በኢትዮጵያ ለሚገኙ የተፋሰሱ ሀገራት አምባሳደሮችና ዲፕሎማቶች ገለፃ አድርገዋል፡፡ […]

ዙማ ከፖሊስ ጋር ድብብቆሽ በቃኝ አሉ፡፡

አዲስ አበባ ፣ ሃምሌ 1፣ 2013 የቀድሞው የደቡብ አፍሪካ ፕሬዚዳንት ጃኮቭ ዙማ ለፖሊስ እጃቸውን መስጠታቸው ተሰማ፡፡ የተመሰረተባቸውን የሙስና ክስ ችሎት ቀርበው እንዲያስረዱ የሀገሪቱ ፍርድ ቤት የሰጠውን ትዕዛዝ ባለማክበር የ15 ወራት እስር የተፈረደባቸው ዙማ ቅጣቱ እንዲቀርላቸው አቤት ብለው ነበር፡፡ የተወሰነባቸውን ቅጣት እንዲፈፅሙ ሲጠየቁ አሻፈረኝ ብለው የነበሩት ፕሬዚዳንቱ ፖሊስ በሃይል ይዞ ወደ አስር ቤት ሊወስዳቸው በሚዘጋጅበት በገዛ […]