loading
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን በሀገር ውስጥና በውጭ የነበሩት ሲኖዶሶች በአንድ ሲኖዶስ ለመመራት ተስማሙ

ባለፉት 27 ዓመት በሁለት ሲኖዶስ ስትመራ የቆየችውን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስትያን ወደ አንድ ለማምጣት የሰላምና የእርቅ ጉባዔው በዋሸንግተን ደብረ ሀይል ቅዱስ ገብርዔል ቤተክርስቲያን ባለፈው እሁድ የሁለቱም ልኡካን አባቶች በተገኙበት የጋራ ጸሎትና የመክፈቻ መርሐ ግብር ተጀምሯል። በእስካሁኑ ውይይታቸው በአንድ ሲኖዶስ ለመመራት ከስምምነት ላይ መድረሳቸው ነው የተነገረው። በተጨማሪም “የሀገር ቤት ሲኖዶስ” እና “ስደተኛ ሲኖዶስ” የሚባለውን ለማስቀረት ተስማምተዋል። ይህ […]

አሁን የኢትዮጵያ፣ ኤርትራና የተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች የሶስትዮሽ ጉባኤ በአቡ ዳቢ እየተካሄደ ነዉ

በዚህ የሶስትዮሽ ጉባኤ ላይ የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ፣ የኤርትራው ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ እና የተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች አልጋወራሽ ሼክ መሀመድ ቢን ዛይድ አል ነኸያን በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ። በሶስትዮሽ ውይይት ላይ የሶስቱ ሀገራት የኢንቨስትመንት ግንኙነት እንዲሁም ቀጠናዊ ጉዳዮች ይነሳሉ ተብሎ ይጠበቃል።

አቶ ሚሊዮን ማቲዮስ የደቡብ ክልል ርዕሰ መስተዳደር ሆነው ተሾሙ

የደቡብ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ክልል ምክር ቤት በ5ኛ ዙር 3ኛ ዓመት የስራ ዘመን 7ኛ መደበኛ ጉባዔው አቶ ሚሊዮን ማቲዮስን የክልሉ ርዕሰ መስተደሳድር አድርጎ ሾሟል። አቶ ሚሊዮን ቃለ መሃላ በመፈፀም ቀደም ሲል ክልሉን በርዕሰ መስተዳድርነት ሲያገለግሉ ከነበሩት አቶ ደሴ ዳልኬ ኃላፊነቱን ተረክበዋል። አቶ ሚሊዮን ማቲዮስ በቅርቡ ክልሉን የሚያስተዳድረው የደቡብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ/ደኢህዴን/ ምክትል ሊቀመንበር ሆነው […]

ከብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስና ከብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሪዮስ ቀጣይ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን ፓትሪያሪክ ማን ይሆናል?

ይህ ጥያቄ ከእርቁ በኋላ የሚመለስ ቢሆንም ዲያቆን ዳንኤል ክብረት ግን ለቢቢሲ አማርኛዉ እንደተናገሩት ከሁለቱ ፓትርያሪኮች መካከል የስልጣን መንበሩ ላይ መቀመጥ ያለበት የሚለው ጥያቄ ማነቆ ሆኖ የቆየ ቢሆንም እርሱን አሁን መፍታት ብዙም አይገድም ብለዋል። ብፁዕ አቡነ ማቲያስ የአስተዳደሩን ስራ እየሰሩ፤ አቡነ መርቆሪዮስን ደግሞ በመንበራቸው ሆነው ከአስተዳደሩ ስራ ግን ገለል እንዲሉ ስማቸውም በቅዳሴ እየተጠራ በሲኖዶሱም እየተገኙ እንዲቀጥሉ […]

በስብሰባ መሀል ዘና በሉና ተሸለሙ

ዛሬ ጠ/ሚኒስትሩ ከመምህራን ጋር የነበራቸው ቆይታ የቻይና ጉዞ ሽልማቶችም እንደነበሩት ሰምተናል፡፡ ዶ/ር አብይ ከጋበዟቸው እና ወደ መድረክ ከወጡት ስምንት መምህራን “ፑሽ አፕ” ከጠ/ሚኒስትሩ ጋር የሰሩ እና ያልደከሙ ሦስት መምህራን ቻይና ለ 15 ቀን ስልጠና እንደሚሄዱ ተነግሯቸዋል፡፡ በወንዶቹ ሳያበቃ ለተመሳሳይ ውድድር ሲጋበዙ ተሸቀዳድመው የወጡ ከ36 በላይ ሴቶችም ለሁሉም የቻይና የጉብኝት ዕድል እንደተሰጣቸው ሰምተናል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በወርቅ ሜዳልያ ከተመረቁ 400 ተማሪዎች ጋር ተገናኙ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በወርቅ ሜዳልያ ከተመረቁ 400 ተማሪዎች ጋር ተገናኙ፡፡ ተመራቂዎቹንም አበረታትተዋል፡፡ የወርቅ ሜዳልያ ተሸላሚ ተማሪዎቹም ለክቡር ጠቅላይ ሚኒስትሩ ያላቸውን ክብር፣ ፍቅር እና አጋርነት ገልጸዋል፡፡

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ቡናን በአለም ገበያ ላስተዋዉቅ ነዉ አለ

” አለም አቀፍ የቡና ቀን በምድረ ቀደምት” በሚል ቡናን ለማስተዋወቅ የመክፈቻ ፕሮግራም ተዘጋጅቷል፡፡ በአየር መንገዱ የኮርፖሬ ት ኮሙኒኬሽን ኦፊሰር አቶ አደፍርስ ታዬ ለአርትስ ቲቪ እንደተናገሩት በፕሮግራሙ የአየር መንገዱ ሰራተኞች፣የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን እና በቱሪዝም ዘርፍ የሚሰሩ ተቋማት በመገኘት የኢትጵያን ቡና በአለም ገበያ ማስተዋወቅን በተመለከተ ይመክራሉ ፡፡

ዛሬ ኢትዮ ቴሌኮምን በዋና ሥራ አስፈጻሚነት ለመምራት ኃላፊነታቸውን የተረከቡትን ወ/ት ፍሬሕይወት ታምሩን እናስተዋውቃችሁ

ዛሬ ኢትዮ ቴሌኮምን በዋና ሥራ አስፈጻሚነት ለመምራት ኃላፊነታቸውን የተረከቡትን ወ/ት ፍሬሕይወት ታምሩን እናስተዋውቃችሁ፡፡ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በኢንፎርሜሽን ሲስተም በመጀመርያ ዲግሪ ተመርቀዋል፣ እንግሊዝ ከሚገኘው ኦፕን ዩኒቨርሲቲ ደግሞ በቢዝነስ አድሚኒስትሬሽን የማስተርስ ዲግሪ አግኝተዋል፡፡ አዲሷ ዋና ሥራ አስፈጻሚ በቴሌኮም ዘርፍ ለስምንት ዓመታት የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂውን ከመምራት አንስቶ፣ እስከ ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚነት ድረስ ማገልገላቸውን ከኢትዮ ቴሌኮም ሕዝብ ግንኙነት ክፍል […]

ማይክ ፖምፒዮ የኢራንን መሪዎች ከማፊያ ጋር አመሳስለዋቸዋል

የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚንስትር ማይክ ፖምፒዮ የኢራን መሪዎች ከመንግስትነት ይልቅ የማፊያ ባህርይ ጎልቶ ይንጸባረቅባቸዋል ብለዋል፡፡ ሮይተርስ እንደዘገበው ፖምፒዮ ለዚህ አባባላቸው በሀገሪቱ ያለውን ሰፊ ሀብትና የመሪዎቹን በሙስና መዘፈቅ በማሳያነት አቅርበዋል፡፡ ፖምፒዮ ካሊፎርኒያ ውስጥ ባደረጉት ቅስቀሳ የሚመስል ንግግር ኢራናውያን የሀገራቸውን ዕጣ ፈንታ ራሳቸው መወሰን አለባቸው፤ እኛ አሜሪካውያንም ከጎናቸው እንቆማለን ብለዋል፡፡ በአሁኑ ወቅት የሁለቱ ሀገራት መሪዎች በየፊናቸው አንዱ […]

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በተለያዩ ምክንያት ከስራ የተባረሩ 42 መምህራንን ወደ ስራ እንዲመለሱ ውሳኔ አስተላለፉ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ ከ50 የተለያዩ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ከተዉጣጡ 3 ሺ 175 መምህራን ጋር እየተወያዩ ነው፡፡ጠቅላይ ሚኒስትሩ እውቀት እና የአካዳሚክ ነጻነት በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ውስጥ ለሚኖር ነጻ አስተሳሰብ ቅድመ ሁኔታዎች መሆናቸውን ተናግረዋል። ዶክተር አብይ ለመምህራኖቹ ጥያቄ በሰጡት ምላሽ በትምህርቱ ዘርፍ የተያዘውን ግብ ለማሳካትም ብቁ መምህራን እና ጥራት ያለው ትምህርት አስፈላጊ መሆኑን ገልጸዋል። ብቃት […]