loading
የኢትዮጵያ አየር መንገድ በ2010 በጀት አመት ከ89 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ አገኘሁ አለ፡፡

ገቢዉ ካለፈዉ አመት ጋር ሲነጻጸር የ1/4ኛ አድገት ማሳየቱንና፤ የተጣራ 6.8 ቢሊዮን ብር ማትረፉንም ተናግሯል፡፡ ዛሬ አየር መንገዱ የዘንድሮውን አመት እቅድ አፈጻጸም አስመልክቶ ባቀረበዉ ሪፖርት እንደጠቆመዉ በዚህ ዓመት በአፍሪካ ሀገራት የነበረዉን አለመረጋጋት፣የንግድ ጦርነት ፣የነዳጅ ዋጋ መጨመር ችግር የነበረ ሲሆን፤ከአየር መንገዱ አጠቃላይ ወጪ 40 በመቶ የሚሆነዉ ለነዳጅ ወጪ ሆኗል፡፡ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ተወልደ […]

አቡዳቢ ከኢትዮጵያ ወደ ኤርትራ የነዳጅ ማስተላለፊያ መስመር ልትዘረጋ ነው ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድና የተባበሩት አረብ ኤሜሬቶች የዓለም አቀፍ ትብብር ሚኒስትር ሪም አል ሃሺሚ አዲስ አበባ ላይ ተገናኝተው በጉዳዩ ዙሪያ ተወያይተዋል። ሚድል ኢስት ሞኒተር የኢትዮጵያ የስራ ኃላፊዎችን ጠቅሶ እንደዘገበው የነዳጅ ማስተላለፊያ መስመሩ ከአዲስ አበባ አሰብ ይዘረጋል ። የጠቅላይ ሚንስትሩ የጽህፈት ቤት ሃላፊ አቶ ፍጹም አርጋ ለሮይተርስ እንደተናገሩት ከአቡዳቢ ጋር የተደረገው ውይይት በኢንቨስትመንት፣በግብርናና በሌሎች ዘርፎች […]

የኢትዮጵያ አየር መንገድ 5 የአፍሪካ አየር መንገዶችን በሽርክና ሊያስተዳድር ነዉ፡፡

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ተወልደ ገብረማርያም እንደተናገሩት የጊኒ አየርመንገድን በ49 በመቶ፣የዛምቢያ አየር መንገድን በ45 በመቶ፣ እንደ አዉሮፓዉያን አቆጣጠር በጥቅምት የሚጀምረዉን የቻድ አየር መንገድን በ49 በመቶ ድርሻ በሽርክና ሊያስተዳድር ነዉ፡፡ የዛምቢያና የኢኳቶሪያል ጊኒ አየር መንገዶችን ደግሞ የአስተዳደራዊ ስራዉን እንዲሰራ በቀረበለት ጥያቄ መሰረት ተቀብሎ በሽርክና ለማስተዳደር መስማማቱን ነዉ አቶ ተወልደ የገለጹት፡፡

በማሊ የተካሄደው ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ በአንጻራዊነት ሰላማዊ ነበር ተባለ፡፡

ምርጫው በወቅቱ የሀገሪቱ ፕሬዝዳንት በኢብራሂም ቡበከር ኬታ እና በተቃዋሚው ሶውማሊያ ሲሴ መካከል ብርቱ ፉክክር ተካሂዶበታል ነው የተባለው፡፡ ዩሮ ኒውስ እንደዘገበው ሀገሪቱን እየመሩ ያሉት ኬታ ለሁለተኛ ጊዜ የማሸነፍ ዕድል እንዳላቸው እየተነገረላቸው ነው፡፡ በተፎካካሪነት እጩ ሆነው የቀረቡት ሲሴ በበኩላቸው ምርጫውን እንደሚያሸንፉ በልበ ሙሉነት ተናግረዋል፡፡ ሲሴ አያይዘውም ገዥው ፓርቲ የምርጫ ኮሮጆዎችን የራሱ ለማድረግ ሞክሯል የሚል ክስ ማቅረባቸው ተሰምቷል፡፡ […]

የኤርትራው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ኦስማን ሳላህና የፕሬዚዳንቱ አማካሪ የማነ ገብረአብ ለይፋዊ የስራ ጉብኝት ሞቃዲሾ መግባታቸዉን ኤርትሪያን ፕሬስ ዘግቧል፡፡

የኤርትራው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ኦስማን ሳላህና የፕሬዚዳንቱ አማካሪ የማነ ገብረአብ ለይፋዊ የስራ ጉብኝት ሞቃዲሾ መግባታቸዉን ኤርትሪያን ፕሬስ ዘግቧል፡፡ በዛሬው ዕለት ወደ ሞቃዲሾ ያቀናው በውጭ ጉዳዩ ሚኒስትሩ የተመራው ልዑክ በሁለትዮሽ እና በቀጠናዊ ጉዳዮች ላይ ውይይት ያደርጋሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡ በውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ የተመራው ልዑክ ወደ ሞቃዲሾ ከማቅናቱ በፊት በኢትዮጵያ ለሁለት ቀናት ቆይታ ማድረጉ ይታወሳል፡፡

ግብጽ አምስት ሰዎችን በእድሜ ልክ እስራት ቀጣች፡፡

የግብጽ ፍርድ ቤት የቀድሞውን የሙስሊም ወንድማማቾች ፓርቲ መሪ ሞሀመድ ባዲን ጨምሮ አምስት ሰዎች በእድሜ ልክ እስራት እንዲቀጡ ወስኖባቸዋል ተብሏል፡፡ አናዶሉ የዜና ወኪል እንደዘገበው አሁን ከአራት አጋሮቻቸው ጋር የእድሜ ልክ እስር የተፈረደባቸው ባዲ በ2013 ከተያዙ በኋላ በተናጠል ፍርድ ቤት ቀርበው የሞት ቅጣት ተወስኖባቸው ነበር፡፡ ፍርድ ቤቱ የቀድሞውን የአቅርቦት ሚኒስትር ባሰም ኡዳን በ15 ዓመት እንዲሁም ሌሎች 3 […]

ኢትዮጵያ ከቱሪስቶች 3. 5 ቢሊየን የአሜሪካን ዶላር አገኝች፡፡

የባህል እና ቱሪዝም ሚኒስቴር የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር አቶ ገዛኸኝ አባተ ለአርትስ ቲቪ እንደተናገሩት በ2010 ዓ.ም ኢትዮጵያን ከጎበኙ 934 ሺ ቱሪስቶች 3.5 ቢሊየን የአሜሪካን ዶላር ገቢ መገኘቱን ተናግረዋል፡፡ ከጎብኝዎች መካከል የቻይና ቱሪስቶች ከፍተኛ ቁጥር ያላቸዉ ሲሆን፤ የእንግሊዝ እና የአሜሪካን ዜግነት ያላቸዉ ቱሪስቶችም በብዛት ሀገራችንን ጎብኝተዋል፡፡ ለገቢዉ መገኘት ሚኒስቴር መስሪያቤቱ ከባለድርሻ አካላትጋር ዘርፉን ለማሳደግ በጋራ መስራቱና የኢትዮጵያ […]

በቢሾፍቱ ከተማ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሊገነባ ነው ፡፡

የኢትዮጵያ አየር መንገድ በቢሾፍቱ ከተማ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሊገነባ መሆኑን አስታወቀ። የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ተወልደ ገብረማርያም ለፋና እንደተናገሩት ፥ አዲስ የሚገነባውን አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታ ለማስጀመር እንቅስቃሴ እየተደረገ ነው። አውሮፕላን ማረፊያውን ለመገንባት የሚያስፈልገውን የቦታ ጥያቄ ለመፍታት ከኦሮሚያ ክልል ጋር ምክክር እየተደረገ መሆኑን አቶ ተወልደ ተናግረዋል። ሊገነባ የታሰበው ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ […]

ኢትዮጵያ የአጼ ቴዎድሮስን ሹርባ ከእንግሊዝ ለማስመለስ ጥያቄ አቀረበች፡፡

እንደ አውሮፓዊያኑ አቆጣጠር በ1868 መቅደላ ላይ በኢትዮጵያና በእንግሊዝ መካከል በተደረገው ጦርነት የእንግሊዝ ወታደሮች ከዘረፏቸው ቅርሶች መካከል የአጼ ቴዎድሮስ ሹርባ ይገኝበታል፡፡ ከዚያን ጊዜ ጀምሮ የንጉሱ ጉንጉን ጸጉር ለንደን ውስጥ በናሽናል አርሚ ሙዚየም ተቀምጦ ይገኛል፡፡ ባለፈው ሚያዚያ ወር የአትዮጵያ አምባሳደር ሙዚየሙን ከገጎበኙ በኋላ የይመለስን ጥያቄ ማቅረባቸውን ተከትሎ ለጊዜው ለጎብኝዎች እይታ ከተቀመጠበት ቦታ ገለል ተደርጓል ሲል ዘ ጋርዲያን […]

በኢትዮጵያ ውስጥ ከሚገኙ የተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች 29 ኢትዮጵያዊያን ተማሪዎች የቻይና መንግስት የሰጠውን ነፃ የትምህርት እድል አገኙ፡፡

ዥንዋ እንደዘገበው ተማሪዎቹ በማህበራዊ እና በተፈጥሮ ሳይንስ የትምህርት ዘርፎች የድህረ ምረቃ ፕሮግራሞችን የሚከታተሉ ሲሆኑ ከ29 ተማሪዎች ውስጥ የዶክትሬት ዲግሪ ተማሪዎችም ይገኙበታል፡፡ የትምህርት ሚኒስትር ዲኤታ ዶክተር ሳሙኤል ክፍሌ የቻይና መንግስት ለኢትዮጵያዉያን የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች የሰጠው ነፃ እድል በሁለቱ ሃገራት መካከል ያለውን ጠንካራ የዲፕሎማሲ፣ የባህል እና የምጣኔ ሃብት ትስስር ያመለክታል ብለዋል፡፡ በሃገሪቱ የወደፊት እጣ ፋንታ ላይም […]