loading
የዘንድሮ የኢ.ቢ.ሲ የስፖርት ሽልማት በመጪው መስከረም በሸራተን አዲስ እንደሚደረግ ይፋ ሆነ፡፡

በ 2009. ዓ.ም የተጀመረው የኢ.ቢ.ሲ የአመቱ ምርጥ የስፖርት ሽልማት በዘንድሮ አመትም ለሁለተኛ ጊዜ በአምስት ዘርፎች እንደሚያካሄድ ኮርፖሬሽኑ አስታዉቋል፡፡ የኢ.ቢ.ሲ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ አቤል አዳሙ ከስራ አስፈፃሚ ኮሚቴዎች ጋር ዛሬ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ እንደተናገሩት በእግር ኳስ ዘርፍ እና በአትሌትክስ ዘርፍ በሁለቱም ፆታዎች ፤ከአምናው በተለየ ደግሞ የህይወት ዘመን ተሸላሚ ዘርፍም በዘንድሮዉ ሽልማት ተካቷል፡፡ እነዚህን እጩዎች […]

ዛሬ ሰሜን ሸዋ ዞን አንጎለላ ጠራ ወረዳ በጨፋና ቀበሌ በደረሰ የመኪና አደጋ የ16 ሰዎች ህይወት አልፏል፡፡

ዛሬ ሰሜን ሸዋ ዞን አንጎለላ ጠራ ወረዳ በጨፋና ቀበሌ በደረሰ የመኪና አደጋ የ16 ሰዎች ህይወት አልፏል፡፡አደጋዉ የደረሰዉ ከቀኑ ሰባት ሰዓት ፡፡ሲሆን የህዝብ አይሱዙ ከሲኖትራክ ጋር ተጋጭተዉ ነዉ የሰዎች ህይወት ያለፈው ፡፡

ኢንጂነር ሞገስ ጥበቡ የአዲስ አበባ መንገዶች ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ሆነው ተሾሙ፡፡

በኮንስትራክሸን ፕሮጀክት ማኔጅመንት ኢንስቲትዩት በዋና ዳይሬክተርነት እንዲሁም በኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን የኮንትራት አስተዳደር እና በምህንድስና ግዢ ላይ በሃላፊነት ሲያገለግሉ ቆይተዋል። ኃላፊው በቅርቡ የኢትዮጲያ መንገዶች ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ሆነው የተሾሙትን እና የቀድሞ የተቋሙን ኃላፊ ኢንጂነር ሃብታሙ ተገኝን በመተካት ባለስልጣን መስሪያ ቤቱን ይመራሉ፡፡ የአዲስ አበባከተማ አስተዳደር ከንቲባ ፅ/ቤት እንዳስታወቀው የተጀመሩ ፕሮጀክቶችን በአጭር ጊዜ ማጠናቀቅ እና በከተማዋ የመንገድ መሰረተ […]

የኢፌዲሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዶክተር ወርቅነህ ገበየሁ ከጅቡቲ ፕሬዝዳንት ኢስማኤል ኦማር ጊሌ ጋር በጅቡቲ ተወያዩ።

የዉጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በድረ ገጹ እንዳስታወቀዉ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ዶክተር ወርቅነህ ገበየሁ፥ በኢትዮጵያ እና ጅቡቲ መካከል ያለው ግንኙነት በሁኔታዎችና በአጋጣሚ የማይለወጥ ስትራቴጂካዊ ወዳጅነት ነዉ ብለዋል፡፡ ዶክተር ወርቅነህ፥ በድሬዳዋ በተፈጠረው ክስተት የጅቡቲ ዜጎች ህይወታቸውን በማጣታቸው ማዘናቸውን ገልጸዋል፡፡ የተፈጠረው ክስተት የሁለቱን ህዝቦች አጠቃላይ ግንኙነት አያሳይም ያሉት ዶክተር ወርቅነህ፥ ጥፋተኞቹ በቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ እየተደረገ በመሆኑ በሕግ ተገቢውን […]

በ2019 የታዳጊዎች አፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ እየተሳተፈ የሚገኘው የኢትዮጵያ ከ17 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድን የጅቡቲ አቻውን በሰፊ የግብ ልዩነት አሸነፈ፡፡

በማጣሪያው የመጀመሪያ ጨዋታው የኡጋንዳ ቡድንን 1 ለ 0 ማሸነፉ የሚታወስ ሲሆን በሁለተኛ ጨዋታው ጅቡቲን 4 ለ 0 በመርታት ወደ ተከታዩ ደረጃ ለማለፍ የሚያደርገውን ጉዞ አሳምሯል፡፡ የቀይ ቀበሮዎቹን የድል ጎሎች በየነ ባንጃ፤ በረከት ካሌብ፤ ቢንያም አይተን፤ መንተስኖት እንድርያስ አስቆጥረዋል፡፡ እዚሁ ምድብ ኬንያ ደቡብ ሱዳንን 4 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸንፏል፡፡ በቀጣይ መጭው እሁድ ነሃሴ 13 በቻማዚ […]

በአንዳንድ አካባቢዎች እየተፈጠረ ያለው አለመረጋጋት የቱሪዝም ዘርፉ ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ እያሳደረ ነው ተባለ፡፡

ይህ የተባለው የባህል እና ቱሪዝም ሚኒስቴር ትላንት በመስሪያቤቱ በሰጠው መግለጫላይ ነው፡፤ በመግለጫው የቱሪዝም ዘርፍ ሰላም እና መረጋጋትን የሚሻ ዘርፍ እንደመሆኑ በአንዳንድ የኢትዮጵያ ክፍሎች የተከሰቱት ግጭቶች ቱሪስቶችን እና ትውልደ ኢትዮጲያዊያን ዲያስፖራዎችን የሚያሸሽ ነው ተብሏል፡፡ በባህል እና ቱሪዝም ሚኒስቴር ሚኒስትር ወ/ሮ ፎዚያ አሚን ባለፈው ሳምንት በኢትዮጵያ ሶማሌ ክልል የተፈጠረውን ድርጊት ሚኒስቴር መስሪያቤቱ እንደሚያወግዘው ገልፀው ለሰላም እና መረጋጋት […]

የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ተረኛ ችሎት በብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት የስራ ሃላፊ የነበሩት አቶ ተስፋዬ ኡርጌ ላይ ለተጨማሪ ምርመራ ከፖሊስ ከተጠየቀው 14 ቀን 8 ቀን ፈቀደ፡፡

የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ተረኛ ችሎት በብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት የስራ ሃላፊ የነበሩት አቶ ተስፋዬ ኡርጌ ላይ ለተጨማሪ ምርመራ ከፖሊስ ከተጠየቀው 14 ቀን 8 ቀን ፈቀደ፡፡

መቀመጫውን ደቡብ አፍሪካ ያደረገው ዘ በርንተስት የተባለዉ ፋውንዴሽን የቀድሞ የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚንስትር ሀይለማርያም ደሳለኝን የአማካሪ ቦርድ አድርጎ መሾሙን ኦል አፍሪካን ዶት ኮም ዘግቧል፡፡

መቀመጫውን ደቡብ አፍሪካ ያደረገው ዘ በርንተስት የተባለዉ ፋውንዴሽን የቀድሞ የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚንስትር ሀይለማርያም ደሳለኝን የአማካሪ ቦርድ አድርጎ መሾሙን ኦል አፍሪካን ዶት ኮም ዘግቧል፡፡ ፋውንዴሽኑ የአፍሪካን ኢኮኖሚ በአዲስ አስተሳሰብ እና በአዳዲስ ግኝቶች ለማጠናከር የተቋቋመ ነው፡፡

የአማራ ክልል ከፍተኛ አመራሮች ዛሬ መቀመጫዉን አስመራ ካደረገዉ ከአማራ ዲሞክራሲያዊ ኃይሎች ንቅናቄ (አዲኃን) ጋር ይወያያሉ፡፡

አዲኃን ባለፉት ስምንት ዓመታት መቀመጫውን ኤርትራ አድርጎ የኢትዮጵያን የፖለቲካ ስርዓት በመቃወም የትጥቅ ትግል ሲያደርግ የነበረ የፖለቲካ ፓርቲ ነዉ፡፡ የአማራ መገናኛ ብዙሃን እንዳስታወቀዉ አዲኃን ከመንግስት ጋር የሚያደርገዉ ድርድር ምን ጉዳዮች ላይ እንደሚያተኩር አስካሁን አልታወቀም፡፡ የአማራ ክልል ከፍተኛ አመራሮች ትላንት አስመራ መግባታቸዉ ይታወሳል፡፡