loading
የኦሮሚያ የከተሞች ስራ ዕድል ፈጠራና ምግብ ዋስትና ኤጀንሲ በ2011 በጀት ዓመት ስራ አጥና በግል ስራ ላይ ለተሰማሩ ወጣቶች 3.283 ቢሊዮን ብር ለመስጠት አዘጋጅቻለሁ አለ፡፡

በዚህም 1.1 ሚሊዮን ወጣቶችን በ90 ማህበራት ለማደራጀት ተወስኗል፡፡ ከነዚህ መካከል 64 ሺህ የሚሆኑት ከመንግስት ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የሚመረቁ ናቸው፡፡ ለመፍጠር በተዘጋጀው የስራ ዕድል 52205 ሄክታር የከተማና የገጠር መሬት ተዘጋጅቷል፡፡ እንዲሁም 4648 አዳዲስ ሼዶች የሚገነቡ ይሆናል፡፡ የክልሉ ፕሬዝዳንት አቶ ለማ መገርሳ በወቅቱ እንዳሳወቁት ወጣቶች የተፈጠረላቸውን የስራ ዕድል ብቻ ሳይሆን በሃገር የኢኮኖሚ እድገት ላይ ተፅዕኖ ሊያሳድሩ እንደሚችሉ […]

የመጀመሪያው የቴክኖሎጂ ከተማ በባህር ዳር ሊገነባ ነው፡፡

የሳይንስና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ከአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስትና ከአሜሪካው ሀብ ሲቲ ላይቭ ፕሮጀክት ጋር በመተባበር በባህር ዳር ከተማ የመጀመሪያውን የቴክኖሎጂ ከተማ (Technology Hub City) ለመገንባት በሚቻልበት ሁኔታ ላይ የምክክር መድረክ አዘጋጅቷል፡፡ የምክክር መድረኩ በሳይንስና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ነገ ይካሄዳል፡፡ ምክክሩ Ethiopia is the Real WAKANDA በሚል ርዕስ እንደሚካሄድ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር በገፁ ፅፏል፡፡ የቴክኖሎጂ ከተማው በከፍተኛ ወጪ […]

አዲስ አመትን ለማክበር ወደ አዲስ አበባ እየገቡ ያሉ በውጪ ሀገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን በበጎ ፍቃድ አገልግሎት ለመሳተፍ ጥያቄ ማቅረባቸዉን የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ ኢንጂነር ታከለ ኡማ በትዊተር ገጻቸዉ አስታዉቀዋል፡፡

አዲስ አመትን ለማክበር ወደ አዲስ አበባ እየገቡ ያሉ በውጪ ሀገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን በበጎ ፍቃድ አገልግሎት ለመሳተፍ ጥያቄ ማቅረባቸዉን የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ ኢንጂነር ታከለ ኡማ በትዊተር ገጻቸዉ አስታዉቀዋል፡፡ ኢንጂነር ታከለ ዲያስፖራውን በቀጣይም በከተማዋ ልማት ላይ እንዲሳተፍ ጥሪያችንን እናቀርባለን ብለዋል

ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በበርሚንግሃም ዳይመንድ ሊግ በነገው ዕለት ከሰአት በኋላ በተለያዩ ሩጫዎች ይካፈላሉ፡፡

ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በበርሚንግሃም ዳይመንድ ሊግ በነገው ዕለት ከሰአት በኋላ በተለያዩ ሩጫዎች ይካፈላሉ፡፡ በሴቶች 1500 ሜ በ10:22 ሰዓት፤ አክሱማይት እምባዬ ጉዳፍ ፀጋዬ አልማዝ ሳሙኤል በወንዶች 3000 ሜ መሰናክል በ10:33 ሰዓት፤ ጫላ ባዮ በሴቶች 3000 ሜ. በ10:49 ሰዓት፤ እጅጋየሁ ታዬ

ፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ቁጥሩ በውል ያልታወቀ የጦር መሳሪያ በቁጥጥር ስር ማዋሉን ገለጸ፡፡

ፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ቁጥሩ በውል ያልታወቀ የጦር መሳሪያ በቁጥጥር ስር ማዋሉን ገለጸ፡፡ ኢቢሲ እንደዘገበዉ የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ቁጥሩ በውል ያልታወቀ በነዳጅ ቦቴ ሲዘዋወር የነበረ የጦር መሳሪያ በቁጥጥር ስር አውሏል፡፡ በዚህም 1051 ሽጉጦች፣ መጠናቸው ያልታወቁ ጥይቶች እና ወደ ውጪ ሊወጣ የነበር መጠኑ ያልታወቀ ገንዘብ ቁጥጥር ስር መዋሉን የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ገልጿል፡፡

ለአዲስ ዓመት ከውጪ ሀገር ለሚመጡ ኢትዮጵያዉያን ዲያስፖራዎች 25 በመቶ የጤና አገልግሎት ቅናሽ ይደረግላቸዋል ተባለ፡፡

ጤና ጥበቃ ሚኒስቴር በሰው መግለጫ ከ ነሃሴ 14 ቀን 2010 ዓ.ም ጀምሮ የሚመጡ ኢትዮጲያዉያን ዲያስፖራዎች የአገልግሎት ቅናሹ ተጠቃሚ እንደሚሆኑ ተነግሯል፡፡ በጤና ጥበቃ ሚንስቴር የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ዶክተር ተገኔ ረጋሳ በፌደራል እንዲሁም በክልል የጤናውን ዘርፍ በተመለከተ ለሚመጡት ዲያስፖራዎች መረጃ እንዲሰጥ የተዋቀረ የድንገተኛ አስተባባሪ ቡድን መዘጋጀቱን ተናግረዋል፡፡ ዜጎች ወደ ሃገር ቤት ሲመጡ ከሚያገኙት የጤና አገልግሎት ባሻገር […]

የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ በሃገሪቱ አንዳንድ አካባቢዎች የሚስተዋለው የመንጋ ፍትህ እና አላስፈላጊ ሁከት ተቀባይነት የሌለው እና የህግ የበላይነትን አደጋ ውስጥ የሚጥል መሆኑን ገለጹ።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህን ያሉት በ11ኛው እነ 12ኛው ዙር የሰለጠኑ የመከላከያ መኮንኖችን ባስመረቁበት ወቅት ባደረጉት ንግግር ነው። በወቅቱ ባደረጉት ንግግር ድርጊቱ የህግ የበላይነትን የሚነድ በመሆኑ በአስቸካይ ሊቆም እንደሚገባው ገልጸዋል። ህብረተሰቡ በተለይም ወጣቱ የተሳሳተ መረጃን መሰረት በማድረግ ለህግ ቅድሚያ ሳይሰጥ የሚፈጽማቸው ድርጊቶች እየተገነባች ያለችን ሃገር ከማፍረስ ውጭ ዋጋ እንደሌለውም ጠቅሰዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ የህግ የበላይነት ለአንድ […]

ከሁለት ሳምንት በፊት ከትግራይ ክልላዊ መንግሥት ፍቃድ ውጭ ገብተዋል የተባሉ አርባ አምስት የፌደራል ፖሊስ ፀረ-ሽብር ግብረ ኃይል አባላት ከመቀሌ እንዲመለሱ ተደርገዋል

አባላቱ በአሉላ አባነጋ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ በቁጥጥር ስር የዋሉ ሲሆን የመጡበት አላማም እስኪታወቅ ድረስ እንቅስቃሴያቸው ተገድቦ በፌደራል ካምፕ ውስጥ እንዲቆዩ ተደርጎ ነበር። የትግራይ ክልላዊ መንግሥት ኮሚዩኒኬሽን ኃላፊ አቶ ረዳኢ ኃለፎም ከክልሉ አቅም በላይ የሆነ የፀጥታ ችግር ባለመኖሩ የፀረ-ሽብር ግብረ ኃይል አስፈላጊ አለመሆኑን ለቢቢሲ ተናግረዋል። ጨምረውም ክልሉ ድጋፍ የሚጠይቀው ከክልሉ አቅም በላይ የሆነ ነገር ሲያጋጥም ወይም […]

ከስድስት ወራት በኋላ የሁሉም የስኳር ፕሮጀክቶች ግንባታ እንደሚጠናቀቅ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ ተናገሩ፡፡

ዶክተር አብይ ይህንን ያሉት በባህርዳር ከተማ ከብአዴን አመራሮች ጋር ባደረጉት ምክክር ላይ ነው፡፡ ባለፉት 9 ወራት የተሻለ ብሔራዊ መግባባትን ለመፍጠርና ኢኮኖሚያዊ ለውጦችን ለማምጣት ውጤታማ ተግባራት ተከናዉነዋል ብለዋል፡፡ በሀገሪቱ የተሻለ መግባባት ለመፍጠርም ከዲያስፖራው ማህበረሰብ ጋር የነበረውን ግንኙነት የማስተካከልና በሀይማኖቶች ውስጥ የነበረውን መከፋፈል የማጥፋት ስኬታማ ስራዎች ተሰርተዋል ብለዋል፡፡ በኢኮኖሚ ረገድም የውጭ ምንዛሬ በቤታቸው ያከማቹ ዜጐች ወደ ባንክ […]