loading
በዳያስፖራው የተፈጠረው መነሳሳትና የአንድነት ስሜት ቀጣይነት እንዲኖረው ጥረት እየተደረገ ነው ተባለ::

አዲስ አበባ፣ታህሳስ 20፣ 2013 በዳያስፖራው የተፈጠረው መነሳሳትና የአንድነት ስሜት ቀጣይነት እንዲኖረው ጥረት እየተደረገ ነው ተባለ:: የኢትዮጵያ ዳያስፖራ ኤጀንሲ እንዳስታወቀዉ የዳያስፖራዉ ማህበረሰብ በሀገር ልማትና ዕድገት ለማሳተፍ የሚያስችሉ ሥራዎች እየተሠሩ እንደሆነ ገልጿል፡፡ የዳያስፖራ የምክክር መድረክ በደቡብ አፍሪካ በተካሄደበት ወቅት የኤጀንሲዉ ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ሠላማዊት ዳዊት እንዳሉት ዳያስፖራው አባላት በንግድና ኢንስትመንት፣ በዕውቀት ሽግግር፣ በሬሚታንስና በሌሎች ወሳኝ የሀገር ልማት […]

የተማሪዎችን የፈጠራ ውጤቶች በአግባቡ መምራት የሚያስችል ረቂቅ መመሪያ መዘጋጀቱ ተገለፀ::

አዲስ አበባ፣ታህሳስ 23፣ 2013 የተማሪዎችን የፈጠራ ውጤቶች በአግባቡ መምራት የሚያስችል ረቂቅ መመሪያ መዘጋጀቱ ተገለፀ:: የትምህርት ሚኒስቴር በሳይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በምህንድስና፣ በጥበብና ሂሳብ ዘርፍ የሚቀርቡ የተማሪዎችን የፈጠራ ስራዎች ከዚህ በፊት ከነበረው አሰራር ይበልጥ አጠናክሮ ለማስቀጠል ረቂቅ መመሪያ ማዘጋጀቱን አስታውቋል፡፡ መመሪያው ተወዳዳሪዎች በተቀመጠላቸው መስፈርት መሰረት የፈጠራ ስራዎቻቸውን እንዲያቀርቡና አሸናፊዎች በማያሻማ መልኩ ተለይተው ተገቢውን ማበረታቻ እንዲያገኙ የሚያግዝ መሆኑ ነው […]

በጋምቤላ ክልል በሰለጠነ ባለሙያ የወለዱ እናቶች ሽፋን 40 በመቶ መሆኑ ተገለፀ::

አዲስ አበባ፣ታህሳስ 23፣ 2013 በጋምቤላ ክልል በሰለጠነ ባለሙያ የወለዱ እናቶች ሽፋን 40 በመቶ መሆኑ ተገለፀ:: በክልሉ የእናቶችና ጨቅላ ህፃናትን ጤናና የስርዓተ ምግብ ሁኔታን ለማሻሻል ያለመ የንቅናቄ መድረክ ተካሂዷል፡፡ በዚህ ወቅት የጤና ሚኒስትሯ ዶክተር ሊያ ታደሰ እንዳሉት በክልሉ በሰለጠነ ባለሙያ የሚወልዱ እናቶች ሽፋን 40 በመቶ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡ ሚኒስትሯ የህጻናት ክትባት መሻሻል ቢታይበትም አሁንም ዝቅተኛ ሽፋን እንዳለው […]

የአርቲስት ሃጫሉ ሁንዴሳን ግድያ ተከትሎ በኦሮሚያ ክልል በተከሰተ የፀጥታ መደፍረስ 123 ሰዎች ሲገደሉ 500 ሰዎች የአካል ጉዳት ደርሶባቸዋል ተባለ::

አዲስ አበባ፣ታህሳስ 23፣ 2013 የአርቲስት ሃጫሉ ሁንዴሳን ግድያ ተከትሎ በኦሮሚያ ክልል በተከሰተ የፀጥታ መደፍረስ 123 ሰዎች ሲገደሉ 500 ሰዎች የአካል ጉዳት ደርሶባቸዋል ተባለ:: የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን የምርመራውን ግኝቶች ይፋ ባደረገበት ወቅት በወንጀሉ የተሳተፉ ሰዎች ያደረሱት ጥቃት በሰብአዊነት ላይ የተፈጸመ ወንጀል ባሕርያትን የሚያሟሉ መሆናቸውን አረጋግጧል፡፡

ተላላፊ በሽታዎችን ለመከላከል የጤና ኤክስቴንሽን ወሳኝ ሚና እያበረከተ መሆኑ ተገለጸ::

አዲስ አበባ፣ታህሳስ 26፣ 2013 ተላላፊ በሽታዎችን ለመከላከል የጤና ኤክስቴንሽን ወሳኝ ሚና እያበረከተ መሆኑ ተገለጸ:: የግልና አካባቢ ንጽህናን በአግባቡ በመጠበቅ የተላላፊ በሽታዎችን ስርጭት ለመቀነስ ለጤና ኤክስቴሽን ፕሮግራም የተሰጠው ትኩረት ውጤት እያመጣ መሆኑ ተገልጿል፡፡ የግልና የአካባቢ ንጽህናን ጨምሮ 19ኙ የጤና ኤክስቴንሽን ፓኬጆችን ተግባራዊ ያደረጉ ከ900 የሚበልጡ ግንባር ቀደም ቤተሰቦች ትናንት በባሌ ጎባ ተመርቀዋል። በግንባር ቀደም ቤተሰቦች ምረቃ […]

የላልይበላ ከተማ አስተዳደር የገና በዓል በሰላም እንዲጠናቀቅ አስፈላጊውን ዝግጅት አድርጌያለሁ አለ::

አዲስ አበባ፣ታህሳስ 28፣ 2013 የላልይበላ ከተማ አስተዳደር የገና በዓል በሰላም እንዲጠናቀቅ አስፈላጊውን ዝግጅት አድርጌያለሁ አለ:: የደብረ ሮሃ ቅዱስ ላልይበላ ዓመታዊ ክብረ በዓል በሰላም እንዲጠናቀቅ አስፈላጊው ቅድመ ዝግጅት ተደርጎ እየተሠራ መሆኑን ነው የከተማ አስተዳደሩ የገለፀው፡፡ የቅዱስ ላልይበላን ዓመታዊ ክብረ በዓል ምዕምናንና ጎብኚዎች ወደ ሥፍራው መግባት ከጀመሩ ቀናት ተቆጥረዋል። ቅድስቲቷ ምድርም በምዕመናንና በጎብኝዎች ተውባለች። የበዓሉን ዝግጅት አስመልክቶ […]

ሴት አመራሮች የላቀ የአመራር ጥበብና በውሳኔ አሰጣጥ የተግባቦታዊ ኪሂል በመጎናፀፍ ተቋማቸውን በብቃት ሊመሩ እንደሚገባ ተገለፀ ፡፡

አዲስ አበባ፣ጥር 03፣ 2013 ሴት አመራሮች የላቀ የአመራር ጥበብና በውሳኔ አሰጣጥ የተግባቦታዊ ኪሂል በመጎናፀፍ ተቋማቸውን በብቃት ሊመሩ እንደሚገባ ተገለፀ ፡፡ በከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ሚኒስቴር አዘጋጅነት ከሁሉም የፌደራል ተቋማት ለተውጣጡ ሴት ሚኒስትሮች፣ ሴት ሚኒስቴር ዴኤታዎች፣ ሴት የፓርላማ ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢዎች፣ ኮሚሽነሮችና በከፍተኛ ሴት አመራር ደረጃ ለሚገኙ አካላት የአመራር ጥበብና ተግባቦታዊ ክሂላቸውን የሚያዳብሩበት ስልጠናና እርስ በርሳቸው የካበተ […]

በመላዉ ዓለም የኮቪድ 19 ክትባት መሰጠት መጀመሩ ኢትዮጵያን ከቫይረሱ እንዳይጠነቀቁ ሊያደርግ አይገባም::

አዲስ አበባ፣ጥር 03፣ 2013 በመላዉ ዓለም የኮቪድ 19 ክትባት መሰጠት መጀመሩ ኢትዮጵያን ከቫይረሱ እንዳይጠነቀቁ ሊያደርግ አይገባም ሲሉ አርትስ ያነጋገራቸዉ በሚሊኒየም የኮቪድ 19 ኬር ሴንተር የነርስኒግ ዳይሬክተር ሲስተር ንጋት ወ/ማርያም አሳሰቡ ፡፡ በማዕከሉ ቀደም ሲል ከነበረዉ የታማሚዎች ቁጥርና የፅኑ ህክምና  የሚያስፈልጋቸዉ ሰዎች ቁጥር መበራከታቸዉን ያስታወሱት ሲስተር ንጋት ፤የኮቪድ 19 ክትባት ቢገኝም ለአፍሪካ ብሎም ለኢትዮጵያ ተዳራሽ የመሆኑ […]

በዘንድሮ ሀገራዊ ምርጫ ለሚሳተፉ በጎ ፈቃደኞች ስልጠና እየተሰጠ ነው ::

አዲስ አበባ፣ጥር 04፣ 2013 በዘንድሮ ሀገራዊ ምርጫ ለሚሳተፉ በጎ ፈቃደኞች ስልጠና እየተሰጠ ነው ::የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ከዩ ኤን የልማት ፕሮግራም ጋር በመተባበር ነው በዘንድሮ ሀገራዊ ምርጫ ለሚሳተፉ በጎ ፈቃደኞች ስልጠና የሚሰጠው፡፡ የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ወይዘሪት ብርቱካን ሚደቅሳ ስልጠናው በምርጫው ላይ በተለያዩ ዘርፎች የሚሳተፉ በጎ ፈቃደኞችን አቅም ለማሳደግ አንደሚረዳ ተናግረዋል። ለበጎ ፈቃደኞቹ ክፍተት ባለበት […]

የሃይሌ ማናስ አካዳሚ የ2ኛ ደረጃ አዳሪ ት/ቤት የመጀመሪያ ተማሪዎቹን ተቀበለ::

አዲስ አበባ፣ጥር 04፣ 2013 የሃይሌ ማናስ አካዳሚ የ2ኛ ደረጃ አዳሪ ት/ቤት የመጀመሪያ ተማሪዎቹን ተቀበለ:: የሃይሌ- ማናስ አካዳሚ ውጤት የሆነው ይህ አዲስ ጥራቱን የጠበቀ 2ኛ ደረጃ አዳሪ ት/ቤት በደብረ ብርሃን ተገንብቶ አገልግሎት መስጠት የጀመረ ሲሆን ለመጀመሪያ ጊዜ የ9ኛ ክፍል ተማሪዎቹን ተቀብሏል፡፡ በአዲሱ ካምፓስ ወላጆች በአካል ተገኝተው ልጆቻቸውን ያስመዘገቡ ሲሆን የጉብኝት እና የኮቪድ-19 የጥንቃቄ መመሪያ ገለፃ ላይ […]