loading
ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጅ ኡመር እድሪስ ከዚህ በፊት በአዲስ አበባ የተጠራው የጎዳና ላይ የአፍጥር ፕሮግራም በኛ በኩል እውቅና አልነበረውም አሉ::

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 3 ፣ 2013 ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጅ ኡመር እድሪስ ከዚህ በፊት በአዲስ አበባ የተጠራው የጎዳና ላይ የአፍጥር ፕሮግራም በኛ በኩል እውቅና አልነበረውም አሉ:: ተቀዳሚ ሙፍቲው ይህን ያሉት የኢድ አልፈጥር በዓልን አስመልክተው የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት ባስተላለፉበት ወቅት ነው፡፡ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጅ ኡመር እድሪስ በመልዕክታቸው በዓሉ በሰላም […]

አውሮፓ ህብረት የምርጫ ታዛቢዎቼን ወደ ኢትዮጵያ እልካለሁ ማለቱ ተሰማ::

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 3 ፣ 2013 ህብረቱ ከአሁን ቀደም ምርጫውን ለመታዘብ ያስቀመጣቸው የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት የሚጋፉ ቅድመ ሁኔታዎች በኢትዮጵያ በኩል ተቀባይነት አላገኙም ነበር፡፡ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በሰጠው ሳምንታዊ መግለጫ ስድስተኛውን ሀገራዊ ምርጫ የአውሮፓ ህብረትን ጨምሮ ሩሲያ፣ አሜሪካና ሌሎች ሀገራትና ዓለም አቀፍ ተቋማት ባለሙያዎቻቸውን እንደሚልኩ አስታውቋል፡፡ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ በመግለጫው የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የኢትዮ ሱዳን የድንበር […]

አዲስ የግብይት አማራጭ ይዞ ብቅ ያለው አሪፍ ፔይ በአሜሪካን ሀገር በሚገኘው የፋይናስ ተቋም አሸናፊሆነ፡፡

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 3 ፣ 2013 አዲስ የግብይት አማራጭ ይዞ ብቅ ያለው አሪፍ ፔይ በአሜሪካን ሀገር በሚገኘው የፋይናስ ተቋም አሸናፊሆነ፡፡ አፍሪ ፔይ ሰዎች የዕለት ተዕለት ግብይቶቻቸውን ጨምሮ የመብራትና የውሃ አገልግሎቶችን በቀለሉ መክፈል የሚያስችላቸው የክፍያ ሲስተም ነው፡፡ ይህ ቴክኖሎጂ በተለይም በገጠር አካባቢ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች በቀላሉ ግብይት የሚፈፅሙበት እና የብድር አግልግሎት የሚያገኙበት እንደሆነ ነው የተነገረው፡፡ […]

በምርጫ ወቅት በሴቶች ላይ የሚፈፀሙ ጥቃቶችን እናስቁም በምርጫ ወቅት በሴቶች ላይ የሚፈፀሙ ጥቃቶችን እናስቁም! በሚል ነፃ የሰልክ መስመር ተዘጋጀ::

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 4 ፣ 2013 በምርጫ ወቅት በሴቶች ላይ የሚፈፀሙ ጥቃቶችን እናስቁም በምርጫ ወቅት በሴቶች ላይ የሚፈፀሙ ጥቃቶችን እናስቁም! በሚል ነፃ የሰልክ መስመር ተዘጋጀ:: የኢትዮጵያ ሕግ ባለሙያ ሴቶች ማህበር ከዩ ኤን ኤፍ ፒ ኤ እና ካናዳ ኢምባሲ ጋር በጋራ በመሆን የህግ ድጋፍ እና ማማከር አገልግሎትን ጨምሮ ሌሎችም አገልግሎቶችን በዘላቂነት የሚሰጥ 7711 ነፃ የስልክ […]

በአብዬ በሰላም ማስከበር ግዳጅ ላይ ለተሰማሩ የመከላከያ ሰራዊት አባላት የመጀመሪያ ዙር የኮቪድ- 19 ክትባት ተሰጣቸው፡፡

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 6 ፣ 2013  በአብዬ በሰላም ማስከበር ግዳጅ ላይ ለተሰማሩ የመከላከያ ሰራዊት አባላት የመጀመሪያ ዙር የኮቪድ- 19 ክትባት ተሰጣቸው፡፡ በሱዳን አብዬ ግዛት የሚገኙት የ25ኛ ሞተራይዝድ ሰላም አስለባሪ ሻለቃ አባላት አስትራዜኒካ የተባለው የመጀመሪያ ዙር የኮቪድ 19 መከላከያ ክትባት ነው የተሰጣቸው፡፡ የሻለቃው የህክምና ሃላፊ ሻለቃ ፀሃይ በላቸው ሰራዊቱ እራሱን ከኮቪድ-19 ወረርሽኝ በመከላከል የተሰጠውን አገራዊና […]

ማኅበረሰቡ የኮሮናቫይረስ የመከላከያ መንገዶችን እንዲተገብር የኢትዮጵያ የኅብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት አሳሳበ፡፡

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 6 ፣ 2013 ማኅበረሰቡ የኮሮናቫይረስ የመከላከያ መንገዶችን እንዲተገብር የኢትዮጵያ የኅብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት አሳሳበ፡፡ ኢንስቲትዩቱ በህንድ የተከሰተው አዲስ የኮሮናቫይረስ ዝርያ አሳሳቢ እየኾነ መምጣቱን በማስታወስ ማህበረሰቡ እንዳይዘናጋ አስጠንቅቋል፡፡ የዓለም ጤና ድርጅት በህንድ የተከሰተው የኮሮናቫይረስ ዝርያ ዓለም አቀፍ ስጋት እየሆነ እንደመጣ መግለጹን ኢኒስቲትዩቱ አስታውቋል፡፡ ቫይረሱ እስካሁን በ44 ሀገራት እንደተሰራጨ መገለጹን በማኅበራዊ ትስስር ገጹ አመላክቷል፡፡ […]

በሱዳን በኩል ወደ ሀገር ሊገባ ሲል የተደመሰሰው የህወሃት ቡድን

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 6 ፣ 2013 ከሱዳን በመነሳት በማይካድራ አድርገው ወደ ሀገር ሊገቡ የነበሩ 320 የህወሃት ሀይል አባላት ተደመሰሱ፡፡ የህብረት ዘመቻ ዋና መምሪያ ሀላፊ ተወካይ ብርጋዴር ጄኔራል ተስፋዬ አያሌው እንዳሉት ይህ ቡድን በማይካድራ ጭፍጨፋ አድርሶ ወደ ሱዳን ሸሽቶ የነበረ ነው፡፡ ብርጋዴር ጄኔራል ተስፋዬ በሰጡት መግለጫ ቡድኑ ዳግም ተደራጅቶ የተለያዩ የመገናኛ መሳሪያዎችንና መድሀኒቶችን በመያዝ ወደ […]

ኢትዮጵያዊያን የኢትዮጵያ ሳምንት ፌስቲቫልን እንዲጎበኙ ጥሪ ቀረበ።

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 10 ፣ 2013 ኢትዮጵያዊያን የኢትዮጵያ ሳምንት ፌስቲቫልን እንዲጎበኙ ጥሪ ቀረበ።የባህል እና ቱሪዝም ሚኒስትር ዶ/ር ሂሩት ካሣው፣ የከተማ ልማት እና ኮንስትራክሽን ሚኒስትር ኢንጂነር አይሻ መሐመድ እና የሴቶች፣ ወጣቶች እና ሕፃናት ሚኒስትር ፊልሰን አብዱላሂ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድን ጨምሮ ከፍተኛ የስራ ሀላፌዎች በተገኙበት የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።

የኢትዮጵያ ሳምንት በወዳጅነት ፓርክ እየተካሄደ ነው።

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 10 ፣ 2013 የኢትዮጵያ ሳምንት በወዳጅነት ፓርክ እየተካሄደ ነው። በ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሀሳብ አመንጪነት በ 3 ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶች የተዘጋጀው ፌስቲቲቫሉ ሀገሪቱ ያላትን ሀብትና የተፈጥሮ ፀጋ ለማስተዋወቅ እንዲሁም ወደ ኢንቨስትመንት አማራጭ ለመለወጥ ያለመ ነው። በፌስቲቫሉ ላይ የተለያዩ ክልሎች ልዩ መገለጫችን ያሉትን ባህላቸውን እያስተዋወቁበት ይገኛሉ። መሰል ፌስቲቫሎች ከሀገሪቱ ወቅታዊ ሁኔታ አንፃር መዘጋጀታቸው […]

በአዲስ አበባ ድጋፍ ሰጪ አውቶቢሶች ላይ የተወሰደዉ እርምጃ ድጋፍ ሰጪ አውቶቢሶች በታየባቸው ክፍተት የስራ ውል እንዲያቋርጡ ተደረገ::

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 12፣ 2013 በአዲስ አበባ ድጋፍ ሰጪ አውቶቢሶች ላይ የተወሰደዉ እርምጃ ድጋፍ ሰጪ አውቶቢሶች በታየባቸው ክፍተት የስራ ውል እንዲያቋርጡ ተደረገ:: ከ 60 እስከ 70 የሚጠጉ ድጋፍ ሰጪ አውቶቢሶች ባሳዩት ክፍተት ውላቸው ተቋርጦ በሌሎች የመተካት ስራ እየሰራ እንደሆነ የ አዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትራንስፖርት ቢሮ አስታውቋል፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትራንስፖረት ቢሮ ምክትል […]