loading
ዜጎች በምርጫ የሚሳተፉባቸው አማራጭ መንገዶች

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 19 ፣ 2013 በምርጫ ወቅት ዜጎች በንቃት የሚሳተፉባቸው በርካታ አማራጭ መንገዶች መኖራቸውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ ገለጹ፡፡ በሀገራችን ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት እንዲወለድ የዜጎች ንቁ ተሳትፎ እጅግ ወሳኝ ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህንንም በተግባር ሊያረጋግጡ ይገባል ብለዋል፡፡ ዜጎች በምርጫ ወቅት ተሳትፎአቸውን ከሚያረጋግጡባቸው መነገዶች አንዱ ካርድ ወስደው በሰላማዊ መንገድ የሚሆናቸውን ለመምረጥ ራስን ከማዘጋጀት ይጀምራል ነው […]

የገዳ ሥርዓት ለኦሮሞ ነጻነት ፓርቲ ምርጫው በስድስት ወር እንዲራዘም ጠየቀ::

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 20 ፣ 2013 የገዳ ሥርዓት ለኦሮሞ ነጻነት ፓርቲ ምርጫው በስድስት ወር እንዲራዘም ጠየቀ:: በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የተቀመጠውን መስፈርት አላሟሉም ተብለው ፈቃዳቸው ከተሰረዙ ፓርቲዎች መካከል አንዱ የሆነው የገዳ ፓርቲ መጪው ብሔራዊ ምርጫ በስድስት ወር እንዲራዘም ጠየቀ። የገዳ ሥርዓት ለኦሮሞ ነጻነት ፓርቲ-ገዳ ቢሊሱማ ከምርጫ ቦርድ ጋር በጠቅላይ ፍርድ ቤት ሲያካሄድ በነበረው ክርክር ፈቃዱ […]

በሰሜን አሜሪካ በአዉሮፓ በአዉስትራሊያ እና በአፍሪካ የሚገኙ ኢትዮጵያዉያን ዲያስፖራዎች ኢትዮጵያን የሚያፈርሱ አካሄዶችን እንደሚቃወሙ ገለጹ፡፡

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 20 ፣ 2013 በሰሜን አሜሪካ በአዉሮፓ በአዉስትራሊያ እና በአፍሪካ የሚገኙ ኢትዮጵያዉያን ዲያስፖራዎች ኢትዮጵያን የሚያፈርሱ አካሄዶችን እንደሚቃወሙ ገለጹ፡፡ ኢትዮጵያዉያን ዲያስፖራዎች ወቅታዊ የሀገራቸዉን ሁኔታ በተመለከተ ባወጡት የጋራ መግለጫ ፤ አደገኛ የዉስጥ ግጭት እና የዉጭ ከበባና ዛቻ ባለበት በዚህ የታሪክ ወቅት ልዩነታችን ላይ እያተኮርን የምንበታተንብት ጊዜ ሳይሆን፤ የተነሳብንን አደጋ በጥልቀትና አርቆ በማሰብ መርምረን በምን መልኩ […]

የአትሌት ቀነኒሳ በቀለ ቅሬታ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 21 ፣ 2013 አትሌት ቀነኒሳ በቀለ ለኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ቅሬታውን ገለፀ ፡፡ የኢ/ያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን የስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ሚያዚያ 19 ባደረገው 7ኛ መደበኛ ጠቅላላ ስብሰባ ለቶኪዮ ኦሊምፒክ የሚሳተፉ የማራቶን ተወዳዳሪ አትሌቶች በኑከራ ውድድር መምረጥ አስፈላጊ በመሆኑና በፌዴሬሽኑ የቴክኒክ ኮሚቴ፣ በአሰልጣኞችና በአትሌቶቹም ጭምር በጋራ በተደረገ በመሆኑ እንድትሳተፉ ሲል በወንዶች የ12 እንዲሁም በሴቶች የ8 […]

የፖሊስ ልዩ የበዓል ዝግጅት

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 21 ፣ 2013 የስቅለት እና የትንሳኤ በዓላትን ምክንያት በማድረግ ወቅቱን ያገናዘበ የፀጥታ ዕቅድ አውጥቶ ወደ ተግባር መግባቱን የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ፡፡በበዓላት መዳረሻ ወቅቶች ከወትሮው በተለየ ጨምሮ የሚታየውን የሰዎች እና የተሽከርካሪዎች እንቅስቃሴ ተከትሎ የትራፊክ አደጋ እንዳይከሰት እና በተለይም በግብይት፣ በመዝናኛ ሰፍራዎች እና በዕምነት ተቋማት አካባቢ ወንጀሎች እንዳይፈፀሙ ከወትሮው የተለየ ዝግጅት በማድረግ የፀጥታ […]

ለህግ ታራሚዎች የተደረገ ይቅርታ::

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 22 ፣ 2013የአማራ ክልል ከ2 ሺህ በላይ ለሚሆኑ የህግ ታራሚዎች ይቅርታ ማድረጉን ገለጸ የአማራ ክልላዊ መንግስት ለ2ሺህ 705 የህግ ታራሚዎች ይቅርታ ማድረጉን የክልሉ ጠቅላይ አቃቤ ህግ አስታውቋል፡፡ የክልሉ ጠቅላይ አቃቤ ህግ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ አለምሸት ምህረቴ ለኢዜአ እንደገለጹት የክልሉ መንግስት ለታራሚዎቹ ይቅርታ ያደረገው በይቅርታ ቦርዱ ተመርምሮ መስፈርቱን አሟልተው በመገኘታቸው ነው። የይቅርታው […]

ህዝቡ በዓብይ ፆሙ ለሀገር ሠላም ተግቶ ሲፀልይ የነበረውን ተግባር አጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪ ቀረበ::

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 22 ፣ 2013የደቡብ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳደር ርስቱ ይርዳው ህዝቡ በፆም ወቅት ያሳየውን መተዛዘን፣ መከባበርና ለሀገር ሠላምና ደህንነት ተግቶ ሲፀልይ የነበረውን በጎ ተግባር ከፆሙፍቺ በኋላም አጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪ አቅርበዋል። በክልሉ የትንስዔ በዓልን በማስመልከት ለ970 የሕግ ታራሚዎች ይቅርታና የእስራት ቅነሳ መደረጉን የገለፁት አቶ ርስቱ ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች እንኳን አደረሳችሁ መልዕክትም አስተላልፈዋል። ምክትል […]

በአዲስ አበባ አንድ ግለሰብ ስጋ አንቆት ሕይወቱ አለፈ፡፡

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 25 ፣ 2013 በአዲስ አበባ አንድ ግለሰብ ስጋ አንቆት ሕይወቱ አለፈ፡፡ በፋሲካ በአል ቀን ስጋ እየተመገበ የነበረው ወጣት ስጋው አንቆት ሕይወቱ ሊያልፍ ችሏል፡፡ ድንገተኛ የሞት አደጋው የደረሰው በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ካዲስኮ አካባቢ እንደሆነ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ለኢትዮ ኤፍ ኤም ገልጻል፡፡ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን የህዝብ ግኑኝነት የሚዲያ ሀላፊ ዋና […]

በኢትዮጵያ የሚከበረው የአለም የፕሬስ ነፃነት ቀን

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 26 ፣ 2013 የአለም የፕሬስ ነፃነት ቀን መረጃ ለህዝብ ጥቅም በሚል መሪ ሀሳብ ነው ለ30ኛ ጊዜ እየተከበረ የሚገኘው። ከ 30 አመት በፊት በናሚቢያ መከበር የጀመረው የዓለም የፕሬስ ነፃነት ቀን በአለም አቀፍ ደረጃ መንግስታት የፕሬስ ነፃነትን እንዲያከብሩ መነሻ ሆኗል። በኢትዮጵያ የሚከበረውን አለምአቀፉ የፕሬስ ቀን በማስመልከት አዲስ አበባ ውስጥ ውይይት እየተደረገ ነው፡፡ በሀገራችን የፕሬ […]

ማህበረሰቡ በሀሰተኛ መረጃ እንዳይታለል የጠቅላይ ሚሴቴር ፅህፈት ቤት አሳሰበ፡፡

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 26 ፣ 2013 ማህበረሰቡ በሀሰተኛ መረጃ እንዳይታለል የጠቅላይ ሚሴቴር ፅህፈት ቤት አሳሰበ፡፡ ጽህፈት ቤቱ በማህበራዊ ትስስር ገጹ ባሰፈረው ጽሁፍ የወንጀለኞች ቡድን የሀሰተኛ መረጃ እያሰራጨ መሆኑን ደርሰንበታል ብሏል፡፡ የወንጀለኞች ቡድን አባላቱ ከቀድሞ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የግል የኢሜይል አድራሻ የተላከ በማስመሰል መረጃ በመጠየቅ እና ሐሰተኛ ምላሽ በመስጠት ላይ መሆናቸውን አውቀናል ነወ ያለው። በመሆኑም ሁሉም ሰው […]