loading
መሪዎቹ ሜዳልያ ተሸለሙ

በተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች አልጋወራሽ ሼክ መሀመድ ቢን ዛይድ አል ነኸያን ለጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ እና ለኤርትራው ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ በኢትዮጵያና ኤርትራ መካከል ሰላም እንዲሰፍን ላበረከቱት አስተዋፅኦ የሀገሪቱን ፕሬዚዳንታዊ ሜዳሊያ ሸለሙ።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን በሀገር ውስጥና በውጭ የነበሩት ሲኖዶሶች በአንድ ሲኖዶስ ለመመራት ተስማሙ

ባለፉት 27 ዓመት በሁለት ሲኖዶስ ስትመራ የቆየችውን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስትያን ወደ አንድ ለማምጣት የሰላምና የእርቅ ጉባዔው በዋሸንግተን ደብረ ሀይል ቅዱስ ገብርዔል ቤተክርስቲያን ባለፈው እሁድ የሁለቱም ልኡካን አባቶች በተገኙበት የጋራ ጸሎትና የመክፈቻ መርሐ ግብር ተጀምሯል። በእስካሁኑ ውይይታቸው በአንድ ሲኖዶስ ለመመራት ከስምምነት ላይ መድረሳቸው ነው የተነገረው። በተጨማሪም “የሀገር ቤት ሲኖዶስ” እና “ስደተኛ ሲኖዶስ” የሚባለውን ለማስቀረት ተስማምተዋል። ይህ […]

አሁን የኢትዮጵያ፣ ኤርትራና የተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች የሶስትዮሽ ጉባኤ በአቡ ዳቢ እየተካሄደ ነዉ

በዚህ የሶስትዮሽ ጉባኤ ላይ የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ፣ የኤርትራው ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ እና የተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች አልጋወራሽ ሼክ መሀመድ ቢን ዛይድ አል ነኸያን በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ። በሶስትዮሽ ውይይት ላይ የሶስቱ ሀገራት የኢንቨስትመንት ግንኙነት እንዲሁም ቀጠናዊ ጉዳዮች ይነሳሉ ተብሎ ይጠበቃል።

ከብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስና ከብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሪዮስ ቀጣይ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን ፓትሪያሪክ ማን ይሆናል?

ይህ ጥያቄ ከእርቁ በኋላ የሚመለስ ቢሆንም ዲያቆን ዳንኤል ክብረት ግን ለቢቢሲ አማርኛዉ እንደተናገሩት ከሁለቱ ፓትርያሪኮች መካከል የስልጣን መንበሩ ላይ መቀመጥ ያለበት የሚለው ጥያቄ ማነቆ ሆኖ የቆየ ቢሆንም እርሱን አሁን መፍታት ብዙም አይገድም ብለዋል። ብፁዕ አቡነ ማቲያስ የአስተዳደሩን ስራ እየሰሩ፤ አቡነ መርቆሪዮስን ደግሞ በመንበራቸው ሆነው ከአስተዳደሩ ስራ ግን ገለል እንዲሉ ስማቸውም በቅዳሴ እየተጠራ በሲኖዶሱም እየተገኙ እንዲቀጥሉ […]

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በወርቅ ሜዳልያ ከተመረቁ 400 ተማሪዎች ጋር ተገናኙ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በወርቅ ሜዳልያ ከተመረቁ 400 ተማሪዎች ጋር ተገናኙ፡፡ ተመራቂዎቹንም አበረታትተዋል፡፡ የወርቅ ሜዳልያ ተሸላሚ ተማሪዎቹም ለክቡር ጠቅላይ ሚኒስትሩ ያላቸውን ክብር፣ ፍቅር እና አጋርነት ገልጸዋል፡፡

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ቡናን በአለም ገበያ ላስተዋዉቅ ነዉ አለ

” አለም አቀፍ የቡና ቀን በምድረ ቀደምት” በሚል ቡናን ለማስተዋወቅ የመክፈቻ ፕሮግራም ተዘጋጅቷል፡፡ በአየር መንገዱ የኮርፖሬ ት ኮሙኒኬሽን ኦፊሰር አቶ አደፍርስ ታዬ ለአርትስ ቲቪ እንደተናገሩት በፕሮግራሙ የአየር መንገዱ ሰራተኞች፣የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን እና በቱሪዝም ዘርፍ የሚሰሩ ተቋማት በመገኘት የኢትጵያን ቡና በአለም ገበያ ማስተዋወቅን በተመለከተ ይመክራሉ ፡፡

ዛሬ ኢትዮ ቴሌኮምን በዋና ሥራ አስፈጻሚነት ለመምራት ኃላፊነታቸውን የተረከቡትን ወ/ት ፍሬሕይወት ታምሩን እናስተዋውቃችሁ

ዛሬ ኢትዮ ቴሌኮምን በዋና ሥራ አስፈጻሚነት ለመምራት ኃላፊነታቸውን የተረከቡትን ወ/ት ፍሬሕይወት ታምሩን እናስተዋውቃችሁ፡፡ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በኢንፎርሜሽን ሲስተም በመጀመርያ ዲግሪ ተመርቀዋል፣ እንግሊዝ ከሚገኘው ኦፕን ዩኒቨርሲቲ ደግሞ በቢዝነስ አድሚኒስትሬሽን የማስተርስ ዲግሪ አግኝተዋል፡፡ አዲሷ ዋና ሥራ አስፈጻሚ በቴሌኮም ዘርፍ ለስምንት ዓመታት የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂውን ከመምራት አንስቶ፣ እስከ ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚነት ድረስ ማገልገላቸውን ከኢትዮ ቴሌኮም ሕዝብ ግንኙነት ክፍል […]

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በተለያዩ ምክንያት ከስራ የተባረሩ 42 መምህራንን ወደ ስራ እንዲመለሱ ውሳኔ አስተላለፉ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ ከ50 የተለያዩ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ከተዉጣጡ 3 ሺ 175 መምህራን ጋር እየተወያዩ ነው፡፡ጠቅላይ ሚኒስትሩ እውቀት እና የአካዳሚክ ነጻነት በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ውስጥ ለሚኖር ነጻ አስተሳሰብ ቅድመ ሁኔታዎች መሆናቸውን ተናግረዋል። ዶክተር አብይ ለመምህራኖቹ ጥያቄ በሰጡት ምላሽ በትምህርቱ ዘርፍ የተያዘውን ግብ ለማሳካትም ብቁ መምህራን እና ጥራት ያለው ትምህርት አስፈላጊ መሆኑን ገልጸዋል። ብቃት […]

በአለም አቀፍ ደረጃ የሚሰሩ ሆቴሎች ባህልን የሚያንፀባርቅ ገፅታ ሊኖራቸዉ ይገባል ተባለ

ይህ የተባለዉ የካፒታል ኢንተርናሽናል ሆቴል የባህል አዳራሹን ሲያስመርቅ ነው፡፡ በካፒታል ሆቴል የባህል አደራሽ ምረቃ ስነ-ስርዓት ላይ የከተማዋ ከንቲባ ኢንጂነር ታከለ ኡማ እና ምክትል ከንቲባ ዳግማዊት ሞገስ የተገኙ ሲሆን ምክትል ከንቲባዋ ዳግማዊትም ከተማችን አዲስ አበባ ብዙ ባህል አዳራሾች ያስፈልጓታል ፤በባህል ላይ የሚሰሩ ባለሀብቶችንም እናበረታታለን ብለዋል፡፡ የካፒታል ሆቴል ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ አዲስአለም ገብሬ በሆቴላቸዉ ዉስጥ ልዩ […]

የ12ኛ ክፍል የዩኒቨርሲቲ የመግቢያ ፈተና እስከ ሐምሌ 25 ባለዉ ግዜ ዉስጥ ይፋ ይሆናል

የሐገር አቀፍ ትምህርት ፈተናዎች እና ምዘና ኤጀንሲ በስሜ በሀሰት የተከፈቱ የተለያዩ የፌስ ቡክ ፔጆች የ12ኛ ክፍል ፈተና ወጥቷል፡፡ በሚል ያስወሩት ወሬ ሀሰት ነዉ ብሏል፡፡ ኤጀንሲዉ አስከ ሀምሌ 25 ግን የፈተናዉ ዉጤት ይፋ እንደሚሆን ለአርትስ ቲቪ ተናግሯል፡፡ በኤጀንሲዉ የህዝብ ግንኙነትና ኮሙዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ረዲ ሾና ለጣቢያችን ፈተናዉ ገና በእርማት ላይ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ የሀገር አቀፍ ትምህርት […]