loading
ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ ከአሜሪካው ምክትል ፕሬዘዳንት ማይክ ፔንስ ጋር በሁለቱ ሃገሮች ግንኙነት እንዲሁም በአካባቢያዊ ጉዳዮች ላይ ሰፊ ውይይት አድርገዋል

ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ ከአሜሪካው ምክትል ፕሬዘዳንት ማይክ ፔንስ ጋር በሁለቱ ሃገሮች ግንኙነት እንዲሁም በአካባቢያዊ ጉዳዮች ላይ ሰፊ ውይይት አድርገዋል ::

ጠቅላይ ሚኒስትሩ የአሜሪካን ምክትል ፕሬዝዳንት ያነጋግራሉ::

የዉጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በድረገጹ እንዳስታወቀው የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ ከአሜሪካው ምክትል ፕሬዝዳንት ማይክ ፔንስ ጋር በሁለቱ አገሮች ግንኙነት እንዲሁም በአካባቢያዊ ጉዳዮች ላይ በዛሬው ዕለት ይወያያሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ ዶ/ር አብይ በሰሜን አሜሪካ ከሚገኙ የተለያዩ የፖለቲካ አመለካከት ከሚያራምዱ ኢትዮጵያውያን የፓርቲ መሪዎች ጋር የሚነጋገሩ መሆኑ ታውቋል። በትናንትናው ዕለት ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ በአሜሪካ […]

የኢንጀነር ስመኘው በቀለ የቀብር ስነ – ሥርዓትን እሁድ ሀምሌ 22 ቀን 2010 ዓ.ም ይፈጸማል

የኢንጀነር ስመኘው በቀለ የቀብር ስነ – ሥርዓትን እሁድ ሀምሌ 22 ቀን 2010 ዓ.ም ይፈጸማል ፡፡ ብሔራዊ የቀብር አስፈሚ ዐብይ ኮሚቴ ለአርትስ በላከዉ መግለጫ የቀብር ሥነ-ስርአቱ ዕሁድ ሐምሌ 22 ቀን 2010. ከቀኑ 7፡00 ሰአት በአዲስ አበባ ከተማ አራት ኪሎ በሚገኘው በቅድስት ስላሴ ካቴድራል ቤተክርስቲያን ቤተሰቦቻቸው፣ ከፍተኛ የመንግሥት አመራሮች፣ ወዳጅ ዘመዶች፣ የሥራ ባልደረቦች እና መላው ህዝብ በተገኙበት […]

ዛሬ በልደታ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት የቀረቡት የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር ግርማ ካሳ የአራት ቀናት ጊዜ ቀጠሮ ተጠየቀባቸው፡፡

ዛሬ በልደታ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት የቀረቡት የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር ግርማ ካሳ የአራት ቀናት ጊዜ ቀጠሮ ተጠየቀባቸው፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድን በመደገፍ ሰኔ 16 ቀን 2010 ዓ.ም. በመስቀል አደባባይ የተደረገው ሰልፍ ላይ ከፈነዳው ቦምብ ጋር በተያያዘ በቁጥጥር ሥር የዋሉት ኮሚሽነር ግርማ ካሳ ላይ ፍ/ቤቱ የተጠየቀውን ጊዜ ቀጠሮ ተቀብሏል፡፡

መሰረታዊ የንግድ ሸቀጦች ን የምትደብቁ ተጠንቀቁ ተብላችኋል፡፡

መሰረታዊ የንግድ ሸቀጦች ን የምትደብቁ ተጠንቀቁ ተብላችኋል፡፡ ይህንን ያላችሁ የኢፌድሪ የንግድ ሚኒስቴር ነዉ፡፡ ሚኒስቴር መስሪያቤቱ በላከልን መግለጫ ስንዴ ፣ስኳርና ፓልም ዘይት በመንግስት ድጎማ ወደሀገር ዉስጥ እየገባ ቢሆንም ፤ሚኒስቴር መስሪያቤቱ በአዲስ አበባ እና በዙሪያዋ ባደረገዉ አሰሳና በህዝብ ጥቆማ መሰረታዊ ሸቀጦቹ እየተደበቁ እንደሆነ ደርሼበታለሁ ብሏል፡፡ ሚኒስቴሩም መሰረታዊ ሸቀጦች ላይ ህገወጥ ድርጊቶችን የምትፈጽሙ አካላት ከድርጊታችሁ ተቆጠቡ ካልሆነ የሸማቹን […]

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያንን ሁለቱም ፓትርያርኮች በእኩል የአባትነት ክብር እንዲያገለግሉ ተወሰነ።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያንን ሁለቱም ፓትርያርኮች በእኩል የአባትነት ክብር እንዲያገለግሉ ተወሰነ። ከባለፈው ሰኞ ጀምሮ ሲካሄድ የቆየውን የሰላምና የእርቅ ጉባዔው ተከትሎ የተወሰኑ ውሳኔዎች ይፋ ሆነዋል። በዚህ መሰረት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን በአንድ የቅዱስ ሲኖዶስ አመራር እንድተመራ የተወሰነ ሲሆን፥ በሁለቱም ሲኖዶሶች የተላለፈው ቃለ ውግዘት በጋራ ምልዓተ ጉባኤ ይፈታል ተብሏል። የሁለቱም ቅዱሳን ፓትርያርኮች ስም ቤተ ክርስቲያን ባለችበት ዓለም […]

የቅዱስ ሲኖዶሱ ምልዐተ ጉባዔ በዛሬዉ ዕለት በውጭ በሚገኘው ሲኖዶስ ላይ አሳልፏቸዉ የነበሩ ውግዘቶችን እንደሚያነሳ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽህፈት ቤት አስታወቀ።

የቅዱስ ሲኖዶሱ ምልዐተ ጉባዔ በዛሬዉ ዕለት በውጭ በሚገኘው ሲኖዶስ ላይ አሳልፏቸዉ የነበሩ ውግዘቶችን እንደሚያነሳ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽህፈት ቤት አስታወቀ። ፅህፈት ቤቱ በሰጠው መግለጫ ሀገር ውስጥ የሚገኘው ቅዱስ ሲኖዶስ በ1984፣ 1985 እና በ1999 ዓመተ ምህረቶች አሜሪካ በሚገኘው ሲኖዶስ ላይ አሳልፏቸው የነበሩ ውግዘቶችን በቅዱስ ሲኖዶሱ ምልዐተ ጉባዔ ዛሬ እንደሚያነሳ ተናግሯል። በመግለጫው፥ በመጪው ረቡዕ ወደ ሀገር ቤት […]