loading
የባንኮች አጠቃላይ ሀብት አንድ ትሪሊዮን ብር ደረሰ::

የግል ባንኮች ብድር የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከሰጠው መብለጡም ተሰምቷል፡፡ ሪፖርተር እንደዘገበዉ የቀድሞ የብሔራዊ ባንክ ገዥና የአሁኑ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የፋይናንስ ጉዳዮች አማካሪና የባንኩ ዳይሬክተሮች ቦርድ አባል አቶ ተክለ ወልድ አጥናፉ እንደገለጹት፣ አሥራ ስምንቱ የአገሪቱ የግልና የመንግሥት ባንኮች በ2010 ዓ.ም. መጨረሻ ላይ ያስመዘገቡት የሀብት መጠን አንድ ትሪሊዮን ብር ሊደርስ የቻለው በ2002 ዓ.ም. ከነበረበት 167 ቢሊዮን ብር ተነስቶ […]

አቶ በረከት ስምኦንና አቶ ታደሰ ካሳ ከዳሸን ቢራ ቦርድ አባልነት ተሰናበቱ

የዳሸን ቢራ ፋብሪካ የቦርድ አባል የነበሩት አቶ በረከት ስምኦን፣ አቶ ታደሰ ካሳና አቶ ወንድወሰን ከበደ ከቦርድ አባልነት መሰናበታቸውን ዳሽን ቢራ አክሲዮን ማህበር ለአርትስ ቲቪ በላከዉ መግለጫ አረጋግጧል፡፡ መግለጫው ተሰናባቾቹን የቦርድ አባላት የተኩት አዳዲሶቹ አባላትን አሳዉቋል፡፡ አባላቱም የፖሊሲ ጥናትና ምርምር ማዕከል ዋና ዳይሬክተር አቶ አህመድ አብተው፣ በቅርቡ የብሔራዊ ባንክ ገዥ የሆኑት ዶክተር ይናገር ደሴ እና የጥረት […]

በፒያሳ የሚገኘዉ የዳግማዊ አፄ ምኒሊክ ሀውልት እድሳት ተጠናቀቀ::

ለስድስት ወራት በእድሳት ምክንያት ተሸፍኖ የቆየዉ ሀዉልትም በሚቀጥለዉ ሳምንት ለህዝብ ይፋ ይሆናል ተብሏል፡፡ የአዲስ አበባ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ የህዝብ ግኑኝነት ዳይሬክተር አቶ ወርቁ መንገሻ ለአርትስ ቲቪ እንደተናገሩት የቅርስ እድሳቱ ከሴባስቶፖል መድፍ ጋር 5 ሚሊዮን ብር ፈጅቷል ፡፡ ዳይሬክተሩ ለሃውልቱ እድሳት የተያዘለት የዘጠኝ ወር ግዜ ቢሆንም ቀድሞ በስድስት ወር ጊዜ ዉስጥ እድሳቱ እንደተጠናቀቀ ተናግረዋል፡፡ እድሳቱ በአዲስ […]

የአራት ማረሚያ ቤቶች አስተዳዳሪዎች ከሃላፊነታቸው ተነሱ፡፡

ከሃላፊነታቸው የተነሱት የቂሊንጦ ፤ የቃሊቲ፤ የሸዋ ሮቢት እና የድሬዳዋ ማረሚያቤቶች አስተዳዳሪዎች መሆናቸዉን አርትስ ቲቪ ለማወቅ ችሏል፡፡ የፌደራል ማረሚያ ቤቶች አስተዳደር ረዳት የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ አቶ አዲሱ ጴጥሮስ ለ አርትስ እንደለፁት፤ በቅርቡ ታራሚዎች በተለያዩ መገናኛ ብዙሃን ከፍተኛ የሠብዓዊ መብት ጥሠት እንደሚፈፀምባቸው በመናገራቸዉ እና ማረሚያ ቤቱም አስተዳዳሪዎቹ ጋር ችግር እንዳለ በማረጋገጡ ከሃላፊነታቸው እንዲነሱ ተደርጓል፡፡ የቃሊቲ ከፍተኛ ጥበቃ […]

ኤርትራና ሶማሊያ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነታቸውን ለመቀጠል ተስማሙ ፡፡

ሀገራቱ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነታቸውን ለመቀጠል የተስማሙት ከ15 አመታት በኋላ መሆኑን ኤርቲሪያን ፕረስ ዘግቧል፡፡ የኤርትራው ፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ እና የሶማሊያው ፕሬዘዳንት መሃመድ ፋርማጆን ኤምባሲያቸውን ለመክፈትና አምባሳደር ለመሾም ተስማምተዋል፡፡ የኤርትራው ፕሬዝዳንት ኢሳያስ ቀጠናዊ ግንኙነትን ማጠናከር አስፈላጊ ነው ብለዋል፡፡ የሶማሊያው ፕሬዘዳንት መሃመድ ፋርማጆን በበኩላቸው በሁለቱም ሃገራት ዋና ከተሞች በቅርቡ ኢምባሲዎቻችንን ጠብቁ ብለዋል፡፡

ሐምሌ 28 በሚሌኒየም አዳራሽ የቤተክርስትያን አንድ መሆንን አስመልክቶ ልዩ ጉባዔ ይካሄዳል፡፡

ጉባዔዉ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን አራተኛ ፓትሪያሪክ የሆኑት የብፁዕ አቡነ መርቆሪዎስ አቀባበል አንዱ አካል ነዉ ተብሏል፡፡ የጠቅላይ ቤተክህነት ስራ አስኪያጅ አቡነ ዲዮስቆሮስ ዛሬ በሰጡት መግለጫ በሚሊኒየም አዳራሽ ሀምሌ 28 ቀን 2010ዓ.ም የሚደረገዉ ጉባዔ የቤተክርስቲያን ልደት በመሆኑ ታላላቅ የሀይማኖት አባቶች፤ ህዝበ ክርስትያኑ እና ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድን ጨምሮ አምባሳደሮችና የመንግስት ከፍተኛ ባለስልጣናት ይገኛሉ ብለዋል፡፡ በጉባኤዉ […]

ጎንደርን ፍለጋ የተሰኘ መጽሀፍ ተመረቀ፡፡

በጋዜጠኛ ሄኖክ ስዩም የተጻፈዉ ጎንደርን ፍለጋ የጉዞ ማስታወሻ ትላንት ሲመረቅ በክብር እንግድነት የተገኙት የኢትዮጵያ የቱሪዝም ድርጅት ምክትል ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ሰርፀፍሬ ስብሀት እንደተናገሩት ጋዜጠኛ ሄኖክ የጻፈዉ መጽሀፍ ባህልን ታሪክንና ቱሪዝምን የያዘ ነዉ፤ልንጠቀምብት ይገባል ብለዋል፡፡ ጎንደርን ፍለጋ መጽሀፍ ጋዜጠኛዉ በተለያየ አካባቢዎች ባደረጋቸዉ ጉዞዎች የሰማቸዉን ያያቸዉን ታሪኮች አጣርቶ ያስቀመጠበት ነዉ፡፡ በመጽሀፉ ዉስጥ ጎንደርን ፍለጋ በደጃዝማች አያሌዉ […]

የ12ኛ ክፍል መልቀቅያ ፈተና ዉጤት ዛሬ ከሰዓት ይፋ ይሆናል፡፡

154 ሺ 10 ወንዶችና 127 ሺ 964 ሴቶች በድምሩ 281 ሺ 974 ተማሪዎች ፈተናዉን ወስደዋል፡፡ ተማሪዎች ዉጤታቸሁን ለማወቅ በኤጀንሲዉ ድረ ገጽ app.neaea.gov.et በመግባት admission በሚለዉ ዉስጥ የመፈተኛ ቁጥር በመጻፍ go የሚለዉን አንዴ በመጫን ማየት ትችላላችሁ ተብላችኋል፡፡

በምህረት አዋጅ ሰበብ በማረሚያ ቤቶች ተከስቶ የነበረዉ አለመረጋጋት መስከኑን የፌደራል ማረሚያ ቤቶች አስተዳደር አስታወቀ ፡፡

የምህረት አዋጁ ከወጣ በኋላ ምህረት ይገባናል በሚል በተለያዩ ማረሚያ ቤቶች ሁከት ተከስቶ እንደነበርና አሁን ግን በማረሚያ ቤቶች ዉስጥ መረጋጋት መፈጠሩን የፌደራል ማረሚያ ቤቶች አስተዳደር ረዳት የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ አቶ አዲሱ ጴጥሮስ ለአርትስ ቲቪ ተናግረዋል፡፡ አቶ አዲሱ በጠቅላይ አቃቤ ህግ የምህረት አዋጁ ዝርዝር አፈፃፀም መሰረት በምህረቱ ተጠቃሚ የሚሆኑ እና ተጠቃሚ የማይሆኑ ታራሚዎች በግልፅ ይፋ ከሆነ በኋላ […]