loading
የኢንጅነር ስመኘው በቀለን ቤተሰቦችን ለመደገፍ የገቢ አሰባሳቢ ኮሚቴ ተዋቅሯል::

በሀይደሮ ፓወር ዙሪያ የሚያጠኑና ከፍተኛ ዉጤት ለሚያገኙ ተማሪዎች ኢንጅነር ስመኘዉ በቀለ አዋርድ በሚል ለመስጠት እቅድ ተይዟል ተባለ፡፡ የኢንጅነር ስመኘው በቀለን ቤተሰቦችን ለመደገፍ የገቢ አሰባሳቢ ኮሚቴ ተዋቅሯል:: የመንግስት ኮሙኒኬሽን በድረገጹ እንዳስታወቀዉ ሐምሌ 19 ቀን 2010 ዓ.ም በአዲስ አበባ መስቀል አደባባይ በመኪናቸው ውስጥ ህይወታቸው አልፎ የተገኙትን የኢንጅነር ስመኘው በቀለን ቤተሰቦች መደገፍ የሚያስችል የገቢ አሰባሳቢ ኮሚቴ ተዋቅሯል። ኮሚቴው […]

በቀጥታ የዘር ግብይት ሥርዓት ከ 1 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ ማዳን ተቻለ፡፡

የኢትዮጵያ ግብርና ትራንስፎርሚሽን ኤጀንሲ ከግብርና እንስሳት ሃብት ሚኒስቴር ጋር በጋራ በመሆን የቀጥታ የዘር ግብይት ሥርዓትን በተመለከተ ውይይት አካሂዷል፡፡ የቀጥታ የዘር ግብይት ስርዓት በማስረጽ ከዚህ በፊት በዘር አከፋፋይ እና በአርሶ አደሩ ይደርስ የነበረውን ችግር እና ውጣውረድ በማስቀረት ዘር አምራቹን ከአርሶ አደሩ ጋር በቀጥታ በማገናኝት ይባክን የነበረውን የሰው ጉልበት እና ሃብት ማስቀረት ተችሏል፡፡ የግብርናና አንስሳት ሃብት ሚኒስቴር […]

በአክሱም ጽዮን ለሀገራችን ሰላም ምህላ እየተደረገ ነዉ፡፡

በምህላዉ ከ50 ሺህ ሰዉ በላይ እየታደመ እንደሚገኝ በአክሱም ጺዮን የስብከተ ወንጌል ምክትል ሀላፊ በኩረ ትጉሃን ስቡህ ለአርትስ ቲቪ ተናግረዋል፡፡ ከነሐሴ አንድ ጀምሮ የፍልሰታ ጾምን አስመልክቶ የተጀመረዉ ምህላ አስከ ጾሙ ማብቂያ ድረስ ይቀጥላል፡፡፡በአክሱም ፂዮን ሁልጊዜ ወር በገባ ከ1-7 ባሉት ቀናት ምህላ የሚደረግ ሲሆን የፍልሰታ ፆም አስመልክቶ ደግሞ እስከ ጾም ፍቺ ምህላ ይደረጋል ብለዋል፡፡ በኩረ ትጉሃን የዘንድሮዉን […]

የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት ዛሬ አስቸኳይ ጉባኤ እንደሚያካሄድ የምክር ቤቱ አፈ ጉባኤ ዶክተር ታቦር ገብረ መድህን ገለጹ።

አፈ ጉባኤው ዶክተር ታቦር እንዳሉት ምክር ቤቱ ዛሬ ሰባት ሰዓት በሚያካሄደው አስቸኳይ ጉባዔ ከሚመለከታቸው አጀንዳዎች መካከል አዳዲስ የካቢኔ አባላት ሹመትን ማጽደቅ እና ምክር ቤቱ በወረዳ ደረጃ የሚገኙ አስፈጻሚ አካላት አደረጃጀትን የሚመለከት አዋጅም መርምሮ ያጸድቃል ተብሎ ይጠበቃል ብለዋል አፈ ጉባኤ።

የኤርትራው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዑስማን ሳልህ ዛሬ አዲስ አበባ ይገባሉ።

የኤርትሪያን ፕሬስ እንደዘገበዉ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ በቆይታቸው ከኢፌዴሪ ከፍተኛ ባለስልጣናት ጋር ይወያያሉ ተብሎ ይጠበቃል። ጉብኝቱ ዳግም የተጀመረውን የሁለቱን ሃገራት ግንኙነት ወደ ተሻለ ደረጃ ለማድረስ እንደሚያግዝም ታምኖበታል። ኢትዮጵያና ኤርትራ ለ20 አመታት አቋርጠውት የነበረውን ግንኙነት ዳግም መጀመራቸው ይታወሳል። በቅርቡም የኢፌዴሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዶክተር ወርቅነህ ገበየሁና የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ለማ መገርሳ ወደ ኤርትራ በማቅናት ከኤርትራው […]

የኦሮሚያ ሚዲያ ኔትወርክ ስራ አስኪያጅ ጀዋር ሙሃመድ ዛሬ በባሕር ዳር ከሚገኙ ወጣቶች እና አክቲቪስቶች ጋር በአቫንቲ ብሉ ናይል ሆቴል ይወያያል።

የኦሮሚያ ሚዲያ ኔትወርክ ስራ አስኪያጅ ጀዋር ሙሃመድ ዛሬ በባሕር ዳር ከሚገኙ ወጣቶች እና አክቲቪስቶች ጋር በአቫንቲ ብሉ ናይል ሆቴል ይወያያል። ከጃዋር ጋር ፕሮፌሰር ህዝቅኤል ጋቢሳን ጨምሮ ከኦሮሚያ ሚዲያ ኔትወርክ የተገኙ ልዑካንም የሚሳተፉ ሲሆን ኮሎኔል ደመቀ ዘውዱን ጨምሮ አስር ግለሰቦች ከጎንደር እንዲሚገኙ ታውቋል።

አቶ ልደቱ አያሌው ወደ ፖለቲካ ትግሉ ልንመጣ የምንችለው ያፈረሰን የምርጫ ቦርድ እራሱ ከፈረሰ ብቻ ነው አሉ፡፡

ፓርቲ ከሌለኝ በግለሰብ ደረጃ የማደርገው ተሳትፎ ብዙም ጥቅም ይኖረዋል ብዬ አላስብም ብለዋል ለቢቢሲ፡፤ መቀሌ ተዘጋጅቶ በነበረ ጉባኤ መሳተፋቸው ያላስደሰታቸው ወገኖች ዛቻና ማስፈራሪያ እንዳደረሱባቸውና ይህም ለውሳኔ እንዳበቃቸው ተናግረዋል። ለምን መቀሌ ሄዶ ስብሰባ ተካፈለ ብለው ከፍተኛ የሆነ የስም ማጥፋት ዘመቻ ከፍተውብኝ፤ እንገድልሃለን፤ ንብረትሀን እናቃጥላለን የሚሉ መልእክቶች እየደረሱኝ ነው ብለዋል። በድርጅት ደረጃ የሚያደርጉት አስተዋጽኦ እስከሌለ ድረስ፤ ነጻ ሐሳባቸውን […]

የኦሮሞ ነፃ አውጪ ግንባር (ኦነግ) በሚቀጥሉት ሶስተ ቀናት ውስጥ ወደ ኢትዮጲያ ገብቶ ስራ ይጀምራል ተባለ::

በአቶ ዳውድ ኢብሳ የሚመራው ኦነግ ወደአዲስ አበባ ልዑካን እንደሚያሰማራ እና ጽሕፈት ቤቱን ከፍቶ ሰላማዊ የፖለቲካ እንቅስቃሴ እንደሚጀምር የድርጅቱ መሪ አቶ ዳውድ ኢብሳ ለ ቪ ኦ ኤ ተናግረዋል፡፡ የኢትዮጲያ መንግስትም በአስመራ ከሚገኘው የ ኦነግ ድርጅት ጋር በኢትዮጲያ ይልቁንም በኦሮሚያ የሚገኙ የፖለቲካ ፓርቲዎች እንዴት ህዝቡን ባሳተፈ መልኩፖለቲካዊ እንቅስቃሴ ማድረግ እንዳለባቸው ከስምምነት መድረሳቸው ነው የተነገረው፡፡ አቶ ዳውድ ድርጅታቸው […]