loading
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በአሜሪካ

ጠቅላይ ሚኒስትሩ “ግንቡን እናፍርስ ድልድዩንም እንገንባ” በሚል መሪ ቃል በአሜሪካ በሚያደርጉት ቆይታ ከ40 ሺ በላይ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ይታደማሉ ተባለ፡፡ በዋሽንግተንዲሲ፣ በሎሳንጀለስና በሚኔሶታ በሚካሄዱ የድጋፍ ሰልፎችም የተለያዩ ፕሮግራሞች ተዘጋጅተዋል፡፡ በዋሽንግተን ዲሲ በሚደረገዉ የድጋፍ ሰልፍ ማንኛዉም ኢትዮጵያዊና ትዉልደ ኢትዮጵያዊ የሚሳተፍበት ሲሆን ፤በሎሳንጀለስ ደግሞ የጥያቄና መለስ የዉይይት መድረክ ተዘጋጅቷል፡፡ በሚኔሶታ በሚደረገዉ ሶስተኛዉ የጠቅላይ ሚኒስትሩ ቆይታ የተለያዩ ፖለቲካዊ […]

መንግስት ባወጣው የምህረት አዋጅ ተጠቃሚ ለመሆን ከታራሚዎች ምን ይጠበቃል?

መንግስት ባወጣው የምህረት አዋጅ ተጠቃሚ ለመሆን ከታራሚዎች ምን ይጠበቃል? መንግስት ያወጣው የምህረት አዋጅ ከወጣበት ሐምሌ13ቀን 2010 ዓ.ም ጀምሮ ተፈጻሚ ይሆናል ተብሏል፡፡ የምህረት አሰጣጡ ለሚቀጥሉት 6 ወራት ስራ ላይ የሚውል ሲሆን፤ የምህረቱ ተጠቃሚ የሚሆኑ ታራሚዎች የተጠየቁበት ወንጀል እስከ ግንቦት 30 የተፈጸመ ከሆነ ብቻ ነዉ ተብሏል፡፡ የፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ አቶ ብርሃኑ ፀጋዬ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ በእነዚህ […]

የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ ነገ ወደ አሜሪካ ይሄዳሉ

“ግንቡን እናፍርስ ድልድዩንም እንገንባ” በሚል መሪ ቃል የሚያደርጉት ጉዞ በአጠቃላይ በአሜሪካ የሚገኙ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን፥ በሀገራቸው እየተካሄደ ላለው ሁለንተናዊ ለውጥ አካል ሆነው ለሀገሪቱ ልማትና እድገት አስተዋጽኦ እንዲያደርጉ ያለመ ነው ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሎስ አንጀለስ እና በዋሽንግተን ዲ ሲ ከኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ጋር ይወያያሉ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ እስከ ሐምሌ 24 ቀን ድረስ ነው በአሜሪካ ቆይታ የሚያደርጉት። የኢፌዴሪ […]

መሪዎቹ ሜዳልያ ተሸለሙ

በተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች አልጋወራሽ ሼክ መሀመድ ቢን ዛይድ አል ነኸያን ለጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ እና ለኤርትራው ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ በኢትዮጵያና ኤርትራ መካከል ሰላም እንዲሰፍን ላበረከቱት አስተዋፅኦ የሀገሪቱን ፕሬዚዳንታዊ ሜዳሊያ ሸለሙ።

አሁን የኢትዮጵያ፣ ኤርትራና የተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች የሶስትዮሽ ጉባኤ በአቡ ዳቢ እየተካሄደ ነዉ

በዚህ የሶስትዮሽ ጉባኤ ላይ የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ፣ የኤርትራው ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ እና የተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች አልጋወራሽ ሼክ መሀመድ ቢን ዛይድ አል ነኸያን በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ። በሶስትዮሽ ውይይት ላይ የሶስቱ ሀገራት የኢንቨስትመንት ግንኙነት እንዲሁም ቀጠናዊ ጉዳዮች ይነሳሉ ተብሎ ይጠበቃል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በተለያዩ ምክንያት ከስራ የተባረሩ 42 መምህራንን ወደ ስራ እንዲመለሱ ውሳኔ አስተላለፉ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ ከ50 የተለያዩ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ከተዉጣጡ 3 ሺ 175 መምህራን ጋር እየተወያዩ ነው፡፡ጠቅላይ ሚኒስትሩ እውቀት እና የአካዳሚክ ነጻነት በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ውስጥ ለሚኖር ነጻ አስተሳሰብ ቅድመ ሁኔታዎች መሆናቸውን ተናግረዋል። ዶክተር አብይ ለመምህራኖቹ ጥያቄ በሰጡት ምላሽ በትምህርቱ ዘርፍ የተያዘውን ግብ ለማሳካትም ብቁ መምህራን እና ጥራት ያለው ትምህርት አስፈላጊ መሆኑን ገልጸዋል። ብቃት […]