loading
በምህረት አዋጅ ሰበብ በማረሚያ ቤቶች ተከስቶ የነበረዉ አለመረጋጋት መስከኑን የፌደራል ማረሚያ ቤቶች አስተዳደር አስታወቀ ፡፡

የምህረት አዋጁ ከወጣ በኋላ ምህረት ይገባናል በሚል በተለያዩ ማረሚያ ቤቶች ሁከት ተከስቶ እንደነበርና አሁን ግን በማረሚያ ቤቶች ዉስጥ መረጋጋት መፈጠሩን የፌደራል ማረሚያ ቤቶች አስተዳደር ረዳት የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ አቶ አዲሱ ጴጥሮስ ለአርትስ ቲቪ ተናግረዋል፡፡ አቶ አዲሱ በጠቅላይ አቃቤ ህግ የምህረት አዋጁ ዝርዝር አፈፃፀም መሰረት በምህረቱ ተጠቃሚ የሚሆኑ እና ተጠቃሚ የማይሆኑ ታራሚዎች በግልፅ ይፋ ከሆነ በኋላ […]

በሰኔ 16ቱ የቦንብ ፍንዳታ በተጠረጠሩት ላይ የመጨረሻ የምርመራ የሶስት ቀን ተጨማሪ ጊዜ ተሰጠ::

የቀድሞው የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሸን ምክትል ኮሚሽነር ግርማ ካሳን ጨምሮ በሰኔ 16ቱ የድጋፍ ሰልፍ ላይ ከተከሰተው የቦንብ ፍንዳታ ጋር በተያያዘ የስራ ክፍተት አሳይተዋል ተብለው በተጠረጠሩት ላይ 14 ተጨማሪ የምርመራ ቀናት ተጠይቆ የመጨረሻ የሶስት ቀን ጊዜ ብቻ ተፈቅዷል።

የመንግስታቱ ድርጅት የጸጥታው ምክር ቤት በኤርትራ ጉዳይ ላይ መክሯል፡፡

ኤርትራ ከኢትዮጵያ ለቀረበላት የእርቅ ጥያቄ የሰጠቸው አወንታዊ ምላሽ ለሰላም ያላትን ቁርጠኝነት ያሳያል ነው የተባለው፡፡ ታዲያ ለዚህ የሰላም አጋዥነቷ የተጣለባት ማእቀብ እንዲነሳላት ኢትዮጵያ ለተባበሩት መንግስታ ድርጅት ጥያቄ አቅርባ ነበር፡፡ ሲ ጂ ቲ ኤን እንደዘገበው አሁን ላይ ድርጅቱ የኤርትራ ማእቀብ ይነሳ ወይም አይነሳ በሚለው ሀሳብ ዙሪያ ምክክር አድርጓል፡፡ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስዊድን አምባሳደር ኦልፍ ስኩግ እንዳሉት ኤርትራና […]

ማንነታቸው ያልታወቀ 40 የታጠቁ ወታደሮችን ይዞ ትግራይ ክልል የገባ አንቶኖቭ አውሮፕላን በመቀሌ አሉላ አባ ነጋ አውሮፕላን ማረፊያ ተያዘ።

ማንነታቸው ያልታወቀ 40 የታጠቁ ወታደሮችን ይዞ ትግራይ ክልል የገባ አንቶኖቭ አውሮፕላን በመቀሌ አሉላ አባ ነጋ አውሮፕላን ማረፊያ ተያዘ። ምንጮች ለቢቢሲ እንደገለፁት በአውሮፕላኑ ውስጥ የነበሩት የታጠቁ ወታደሮች ተልዕኮና ማንነታቸው ባይታወቅም ኢትዮጵያዊያን እንደሆኑ ታዉቋል። ከሁለት ቀናት በፊት ከሱዳን በኩል ወደ ኢትዮጵያ እንደገባ የተጠረጠረው አንቶኖቭ አውሮፕላንና አሳፍሯቸው የነበሩት 40 የታጠቁ ወታደሮች በመቀሌው የአሉላ አባ ነጋ አውሮፕላን ማረፊያ መያዛቸውን […]

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ በአሜሪካ የነበረን ቆይታ አድካሚ ቢሆንም ስኬታማ ነበር ሲሉ ተናገሩ፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ በአሜሪካ የነበረን ቆይታ አድካሚ ቢሆንም ስኬታማ ነበር ሲሉ ተናገሩ፡፡ በአሁኑ ሰዓት ለመገኛኛ ብዙሀን እንደተናገሩት እንደ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ሁሉ የኤርትራ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን አንድ እንድትሆንም በኃላፊነት እንሰራለን ብለዋል፡፡ ለነበራቸው ቆይታ ድጋፍ ያደረጉትን ሁሉ አመስግነዋል፡፡

በወታደራዊ ስነ ምግባር ጥሰትና ኩብለላ ወንጀሎች ለተከሰሱ የመከላከያ ሰራዊት አባላት ምህረት ማድረጉን የመከላከያ ሚኒስቴር አስታወቀ።

በዚህም የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በቅርቡ ያጸደቀውን የምህረት አዋጅ መሰረት በማድረግ በወታደራዊ የስነ ምግባር ጥሰት ተከሰው በማረሚያ ቤት የሚገኙና ቀደም ሲል ከሃገር የኮበለሉ የሰራዊት አባላት ምህረት ተደርጎላቸዋል ብለዋል። የመከላከያ ኢንዶክትሪኔሽንና የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር ብርጋዴር ጀኔራል ኪዱ አለሙ፥ ለኢዜአ እንደገለጹት መንግስት በሃገር አቀፍ ደረጃ የጀመራቸውን የለውጥ እንቅስቃሴዎች ለማስቀጠል መከላከያ ሰራዊት ለውጡን በመደገፍ እየሰራ ነው። የምህረት አዋጁ […]

በብላቴ ወታደራዊ ማሰልጠኛ የአየር ወለድ አሰልጣኝ የነበረችው መ/አለቃ አይዳ አሌሮ ተፈታች፡፡

ወደ መከላከያ ሠራዊት የተቀላቀለችው በ1997 ዓ.ም የሥልጠና ቦታው ብር ሸለቆ የምልምል ወታደሮች ማሠልጠኛ ነው፡፡ አይዳ በውትድርና ስልጠና ከፍተኛ ውጤት ያመጣች ተመራቂ ናት፡፡ በፓራሹት 27 ጊዜ በመዝለል የምትታወቀው አይዳ በሁርሶ ወታደራዊ ማሰልጠኛ በ2009ዓ.ም ስትሰለጥን ከ1800 ሰልጣኞች አንደኛ መሆኗ ልዩ ያደርጋታል፡፡ በቅርቡ ከሽብር ቡድን ጋር ተገኛኝተሻል ተብላ ክስ ቀርቦባት ነበር፡፡ በተጨማሪም ውስጥ ለውስጥ ሠራዊቱን በማነሳሳት አገር በማስከዳት […]

የነልደቱ አያሌዉ ኢዴፓ ፈረሰ፡፡

የነልደቱ አያሌዉ ኢዴፓ ፈረሰ፡፡ ፓርቲዉ ከ1አመት ከ8 ወር በፊት በቀድሞ የኢዴፓ ፕሬዝደንት ዶክተር ጫኔ ከበደ በፓርቲዉ ላይ በከፈቱት ክስ ምክንያት ፤በብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ምስክርነት ፓርቲዉ በፍርድቤት እንዲፈርስ ተወስኖ እንደነበር አቶ ልደቱ አያሌዉ ለአርትስ ቲቪ ተናግረዋል፡: ሆኖም እንደ አቶ ልደቱ ገለጻ ፍርድቤቱ ያሳለፈዉን ዉሳኔ ለማስቀልበስ አስከ ቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ ድረስ አቤቱታ ብናቀርብም ምላሽ […]

በሀዋሳ የሚገኙ ተፈናቃይ ወገኖቻችን ከዛሬ ጀምሮ ወደ ቀያቸው ይመለሳሉ፡፡

የደቡብ ብሄር ብሄረሰቦች ህዝቦች ክልል መንግስት ርዕሰ መስተዳደር አቶ ሚሊዮን ማቲዎስ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ እንደተናገሩት በሀዋሳ በተለያዩ መጠለያ ጣቢያዎች ከ 1 ወር በላይ የቆዩ ተፈናቃዮች ከዛሬ ጀምሮ ወደ የቀያቸዉ ይመለሳሉ ብለዋል፡፡ አቶ ሚሊዩን ተፈናቃዮቹ የሚመለሱባቸዉ መንደሮች የቀድሞ ሰላማቸዉን ማግኘታቸዉን ተናግረዋል፡፡ ተፈናቃዮቹ እስኪቋቋሙ ድረስ ቤተሰብ ላላቸው በወር 4 ሺ ብር ፤ቤተሰብ ለሌላቸው ደግሞ በወር 2 ሺ […]

የጀዋር መሐመድ የኦሮሚያ ሚዲያ ኔትዎርክ (ኦ ኤም ኤን /OMN ) የአዲስ አበባ ቢሮ የፊታችን እሁድ በይፋ ይመረቃል፡፡

የጀዋር መሐመድ የኦሮሚያ ሚዲያ ኔትዎርክ (ኦ ኤም ኤን /OMN ) የአዲስ አበባ ቢሮ የፊታችን እሁድ በይፋ ይመረቃል፡፡ የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች እንዳስታወቀዉ በሚሊኒየም አዳራሽ የኦ ኤም ኤን ሥራ አስኪያጅ ጃዋር መሀመድን ጨምሮ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት፣ የሀገር ሽማግለዎችና ቄሮዎች በተገኙበት የቢሮ ምረቃና የገቢ ማሰባሰቢያ ፕሮግራም ይካሄዳል ተብሏል፡፡