loading
ድምጽ በመስጠት ላይ እንዳሉ ምጥ የተያዙት ነፍሰጡር እናት በሰላም ተገላገሉ፡፡

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 14፣ 2013 ድምጽ በመስጠት ላይ እንዳሉ ምጥ የተያዙት ነፍሰጡር እናት በሰላም ተገላገሉ፡፡ በአርሲ ዞን ሄጦሳ ወረዳ ነዋሪ የሆኑት ወይዘሮ አበራሽ ጉታ በጠዋቱ ድምጻቸውን ለመስጠት ወደ ሃጤ አንዶዴ ሄጦሳ ዙሪያ ምርጫ ጣቢያ በመምረጥ ላይ እንዳሉ ነበር በምጥ የተያዙት፡፡ በምጥ ላይ እንዳሉ ድምጻቸውን ከሰጡ በኋላ ወደ ህክምና ተቋም በመሄድ በሰላም መገላገላቸውን አማራ ሚዲያ […]

በትግራይ እንደተፈፀመ በተሰማው የአየር ጥቃት የተጎዱ ወገኖችን በፍጥነት ወደ ሕክምና ስፍራ ማድረስ አልተቻለም ተባለ፡፡

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 16፣ 2013 በትግራይ እንደተፈፀመ በተሰማው የአየር ጥቃት የተጎዱ ወገኖችን በፍጥነት ወደ ሕክምና ስፍራ ማድረስ አልተቻለም ተባለ፡፡ ከተጎጂዎቹ መካከል ወደ መቀሌ ሐይደር ሆስፒታል እስካሁን መድረስ የቻሉት አንድ የ2 ዓመት ሕጻን እና 5 አዋቂ ቁስለኞች መሆናቸውን አርትስ ያገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡ አርትስ ቲቪ ወደ አካባቢው ደውሎ ለማጣራት ባደረገው ጥረት ከመቀሌ በስተምዕራብ 25 ኪሎ ሜትር […]

ምርጫው ዓለም አቀፍ መስፈርትን አያሟላም-ባልደራስ::

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 18፣ 2013 ባልደራስ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ ፓርቲ 6ኛው አገር አቀፍ ምርጫ ዝቅተኛውን ዓለም አቀፍ የምርጫ መስፈርት የማያሟላ ነው አለ፡፡ ፓርቲው በፌስቡክ ገፁ ላይ ባሰፈረው ፅሁፍ በተለያዩ ጊዜያት ሳይንሳዊ ጥናቶች አካሂጄ ነው እዚህ መደምደሚያ ላይ ደረስኩት ብሏል፡፡ ምርጫው ችግር እንዳለበት በማሳያነት ካቀረባቸው ምክንያቶች መካከል በድምፅ አሰጣጥ ወቅት የምርጫ አስፈፃሚዎች የገዢው ፓርቲ እንዲመረጥ የሚረዱ […]

ናይጄሪያ ለ12 ዓመታት በዘለቀው ግጭት ከ300 ሺህ በላይ ህፃናት መገደላቸውን የተባበሩት በ መንግስታት ድርጅት ይፋ አደረገ፡፡

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 18፣ 2013 በሰሜናው ምስራቅ የሀገሪቱ ክፍል ለዓመታት በዘለቀው ግጭት በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ ቁጥራቸው ወደ 350 ሺህ ለሚጠጋ ህፃናት ሞት ምክንያት ሆኗል ብሏል ድርጅቱ፡፡ አልጀዚራ እንደዘገበው ከሟቾቹ መካከል የሚበዙት ዕድሜያቸው ከአምስት ዓመት በታች መሆኑን በሪፖርቱ ተመላክቷል፡፡ ቦኩ ሃራም የተባለው ታጣቂ ቡድን እንደ አውሮፓዊያኑ አቆጣጠር በ2009 የተደራጀ ጥቃት ማድረስ ከጀመረ ወዲህ ከ2 ሚሊዮን […]

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ የፖለቲካ ፓርቲዎችን አመሰገኑ

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 21፣ 2013 ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ሰላማዊ ምርጫ እንዲሳካ አስተዋጽዖ ላደረጉ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምስጋና አቀረቡ:: ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከፖለቲካ ፓርቲ ኃላፊዎች ጋር ተገናኝተው መምከራቸውን በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው አስታውቀዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከስድስተኛው ብሔራዊ ምርጫ አንድ ሳምንት በኋላ ዛሬ ጠዋት ከፖለቲካ ፓርቲ ኃላፊዎች ጋር ተገናኝቼ ኢትዮጵያ አሸናፊ ሆና የወጣችበት ሰላማዊ ምርጫ እንዲሳካ ላደረጉት አስተዋጽዖ […]

ሱዳን የሽግግር መንግስትና በተቃዋሚ ሃይሎች የተጀመረው የሰላም ድርድር አሁንም እክል ገጥሞታል ተባለ::

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 21፣ 2013 በ እስካሁን በተደረጉ ውይይቶች በፖለቲካና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች ዙሪያ መግባባቶች ቢኖሩም በማእከላዊ መንግስትና በክልሎች መካከል በሚኖረው የሥልጣን ውክልና መስማማት አልተቻላቸውም፡፡ አጃንስ ፍራንስ ፕሬስ እንደዘገበው የሱዳን ህዝቦች ነፃነት ንቅናቄን ወክለው የሚደራደሩት አማር አሞን ዋና ዋና ሀገራዊ ስምምነቶች ወደፊት በህዝበ ውሳኔ እንዲረጋገጡ እንፈልጋለን ብለዋል፡፡ በተለይ በሁለቱ ሃይሎች መካከል አለመግባባት እንዲካረር ያደረገው ዋነኛ […]

በጅማ ከተማ ለሸማቾች የተላለፈ ማሳሰቢያ!

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 21፣ 2013  የመጠቀሚያ ጊዜያቸው ያለፈ እና የጥራት ደረጃቸው ዝቅተኛ የሆነ ምግቦች በጅማ ከተማ መወገዳቸዉን ባለስልጣኑ አስታወቀ ግምታቸው 260 ሺህ ብር የሆነ የመጠቀሚያ ጊዜያቸው ያለፈና የጥራት ደረጃቸው ዝቅተኛ የሆነ የምግብ ሸቀጦች መወገዳቸውን የኢትዮጵያ ምግብ እና መድሃኒት ቁጥጥር ባለስልጣን አስታዉቋል፡፡ የባለስልጣኑ ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ጅማ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የመድሃኒት ባለሙያ ኢንስፔክተር ሚፍታህ ዝናብ […]

አዲሱ የኮቪድ -19 ዝርያ ደቡብ አፍሪካን እያመሳት ነዉ ፡፡

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 21፣ 2013 ዴልታ የተሰኘው አዲስ የኮሮና ቫይረስ ዝርያ ደቡብ አፍሪካን ክፉኛ እየጎዳት ነዉ ተባለ አዲሱ የኮሮና ቫይረስ ዝርያ መጀመሪያ በህንድ የተገኘ ሲሆን፤ በደቡብ አፍሪካም የዚሁ የኮሮና ቫይረስ ዝርያ አሳሳቢነት ከፍ እያለ በመምጣቱ አዲስ የእንቅስቃሴ ገደብ ለመጣል ተገዳለች፡፡ ሀገሪቱንም በጥር ወር ወደነበረችበት አሳሳቢ ሁኔታ እየመለሳት የሚገኘው ይህ ቫይረስ ባለፉት ሁለት ቀናት ብቻ […]

የፍትህ ስርዓቱን ለማሻሻል ዘርፉን በእውቀት መምራት ያስፈልጋል- ዶክተር ጌዲዮን ጢሞቲዮስ::

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 22፣ 2013 የፍርድ አፈፃፀም መጓተት ችግሮችን ለመፍታት በቴክኖሎጂ የታገዘ አሠራር መተግበር ይገባል ተባለ፡፡ የፌዴራል የፍትህ የህግ ምርምር እና ሥልጠና ኢንስቲትዩት ከባለድርሻ አካላት ጋር በአዲስ አበባ አውደ-ጥናት አካሂዷል። በአውደ-ጥናቱ ላይ  ከፍርድ አፈፃፀም ጋር ያሉ ችግሮች፣ ከአዕምሮ ጤና ህግ ጋር የተያያዙ ጉዳዮች እንዲሁም ባህላዊ የግጭት አፈታት ላይ ያተኮሩ ጥናታዊ ጽሑፎች ቀርበዋል። የፌዴራል ጠቅላይ […]

የመሪያቸው ሸንቃጣነት ያሳሰባቸው ሰሜን ኮሪያዊያን…

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 22፣ 2013 ሰሜን ኮሪያዊያን የመሪያቸውን ክብደት መቀነስ ከጤናቸው ሁኔታ ጋር አያይዘው ሀሳብ ገብቷቸዋል ተባለ፡፡ ለወትሮው በሰፋፊ ልብሶቻቸው ፈርጠም ባለ ሰውነታቸው የሚታወቁት ፕሬዚዳንት ኪም ጆንግ ኡን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ሸንቀጥ ብለው ታይተዋል ነው የተባለው፡፡ ይህ ደግሞ ለሰሜን ኮሪያዊያን እንደ መልካም ዜና እንደማይቆጠር መገናኛ ብዙሃን በስፋት እየዘገቡት ይገኛሉ፡፡ የሀገሪቱ ቴሌቭዥን ጣቢያ በሳምንቱ መጨረሻ […]