loading
ከአማካይ ሰራተኞቹ ክፍያ በ1400 እጥፍ የሚበልጠው ስራ አስኪያጅ ደመወዝ…

አዲስ አበባ፣ የካቲት 14፣ 2014 አፕል ኩባንያ ሰራተኞቹ ገቢያችን ከኑሯችን አልመጣጠን አለ የሚል ቅሬታ በሚያሰሙበት ወቅት የዋና ስራ አስፈፃሚው ቲም ኩክ ገቢ በ500 ፐርሰንት ማድረጉ በርካቶቸን እያነጋገረ ነው፡፡ ዋና ስራ አስፈጻሚው ባለፈው ዓመት ከደመወዝ ጭማሪ፣ ከጥቅማጥቅም፣ እንዲሁም በጉርሻ መልክ ወደ ኪሳቸው የገባው ገንዘብ ሲሰላ አንድ አማካይ የመስሪያ ቤቱ ሰራተኛ ከሚያገኘው በ1,400 እጥፍ ይበልጣል ነው የተባለው፡፡ […]

የግል ባንኮች ለቀጣዩ ፉክክር ራሳችሁን አዘጋጁ- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 15፣ 2014 በኢትዮጵያ የሚገኙ የግል ባንኮች ራሳቸውን ለውድድር እንዲያዘጋጁ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ አሳሰቡ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተገኝተው ከምክር ቤት አባላት ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡ በዚህ ወቅት በሰጡት ማብራሪያ የግል ባንኮች በዘርፉ እድገት ያስመዘገቡ ቢሆንም አሁንም ብዙ ስራዎች እንደሚጠብቃቸው ገልጸዋል፡፡ በተለይ እስካሁን የግል ባንኮች የውጭ ሀገራት የፋይናንስ ተቋማት ፈቃድ […]

በአሁኑ ወቅት በሀገራችን ትልቁ ፈተና የዋጋ ግሽበት መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስተር ዐቢይ አህመድ ተናገሩ::

አዲስ አበባ፣ የካቲት 15፣ 2014 የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ባለፉት ስድት ወራት በጦርነት፣ በኮቪድ-19 እንዲሁም በተለያዩ ሰው ሰራሽና የተፈጥሮ አደጋዎች ከፍተኛ ፈተና ደርሶበታል ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፡፡ በዚህም ህዝቡ ገዝቶ መብላት እስኪቸገር ድረስ በኑሮ ውድነት ተሰቃይቷል በማለትም የችግሩን አስከፊነት አስታውሰዋል፡፡ የዋጋ ግሽበት በመላው ዓለም እየጨመረ መሆኑ ቢታወቅም እንደኛ ድሃ በሆኑ ሀገራት ግን ችግሩ ሰፊ ጉዳት ያደርሳል ብለዋል፡፡ለዋጋ […]

በጦርነት የወደሙ ከተሞችን መልሶ ለማቋቋም 58 ከተሞች የጥምረት ስምምነት መፈራረማቸውን የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር ገለጸ።

አዲስ አበባ፣ የካቲት 15፣ 2014 በጸጥታ ችግር ጉዳት የደረሰባቸውን ከተሞች መልሶ የመገባንት ሂደት በተፋጠነ መልኩ ለማስኬድ የሚያግዝ አሰራር መዘርጋቱንም አስታውቋል። ሚኒስቴሩ የበጀት ዓመቱት የመጀመሪያ ስድስት ወራት የስራ አፈጻጸም የገመገመ ሲሆን፤ በቤቶች ግንባታ፣ በመሬት አቅርቦትና የግንባታውን ዘርፍ በማዘመን፣ ከተሞችን ለነዋሪዎች የተሻለና ምቹ በማድረግ የአሰራር ማዕቀፍ መዘርጋቱ ተገልጿል። የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ፋንታ ደጄን እንዳሉት፤ […]

አሜሪካ የትግራይ ታጣቂዎች በአማራ ክልል የፈጸሟቸው ዘግናኝ ድርጊቶች በእጅጉ አሳስበውኛል ስትል ገለጸች፡፡

አዲስ አበበ፣ የካቲት 16፣ 2014 አሜሪካ የትግራይ ታጣቂዎች በአማራ ክልል የፈጸሟቸው ዘግናኝ ድርጊቶች በእጅጉ አሳስበውኛል ስትል ገለጸች፡፡ የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአመንስቲ አንተርናሽናልን ሪፖርትን መነሻ አድርጎ ባወጣው መግለጫ በክልሉ አስገድዶ መድፈርን ጨምሮ የተፈጸሙ በርካታ ወንጀሎች አሳሳቢ ናቸው ብሏል፡፡መግለጫው አክሎም በንጹሃን ዜጎች ላይ የሚፈጸመው አሰቃቂ ግፍና ወንጀል በሚገባ ተጣርቶ የድርጊቱፈጸሚዎች ተጠያቂ እንዲሆኑ ጥር አቅርቧል፡፡ የትኛውም የታጠቀ […]

የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ባበለጸጋቸው ስርዓቶች ውስጥ የሚተገበሩ ከ200 በላይ አገልግሎቶች በኦንላይን እየተሰጡ መሆኑን ገለጸ።

አዲስ አበበ፣ የካቲት 16፣ 2014 የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ባበለጸጋቸው ስርዓቶች ውስጥ የሚተገበሩ ከ200 በላይ አገልግሎቶች በኦንላይን እየተሰጡ መሆኑን ገለጸ። ተጨማሪ 45 የመንግስት አገልግሎቶችን በኦንላይን ለመስጠት የሚያስችሉ ስርዓቶች ለምተው መመረቃቸውን ሚኒስቴሩ አስታውሷል፡፡ሚኒስቴሩ ከሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ኤጀንሲ ጋር አገልግሎቶቹ ቀጣይነት ባለው መልኩ እንዲተገበሩ ለማድረግ በጋራ ለመስራት የሚያስችላቸውን ስምምነት ተፈራሟል፡፡ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታዋ ሁሪያ አሊ የመንግስት አገልግሎቶችን […]

ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ኩባንያ በኢትዮጵያ ጥራት ያለው የቴሌኮም አገልግሎት ለመሥጠት እየሰራሁ ነው አለ፡፡

አዲስ አበበ፣ የካቲት 16፣ 2014 ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ኩባንያ በኢትዮጵያ ጥራት ያለው የቴሌኮም አገልግሎት ለመሥጠት እየሰራሁ ነው አለ፡፡ ኩባንያው ይህን የገለጸው በ100 ሚሊዮን ዶላር ወጪ ያስገነባቸውን መሰረተ ልማቶችና የዳታ ቤዝ ማእከሉን ለጋዜጠኞች ባስጎበኘበት ወቅት ነው፡፡ ሳፋሪኮም በኢትዮጵያ ጥራት ያለው የቴሌኮም አገልግሎት ለመሥጠት እየሰራ መሆኑን የኩባንያው የውጭ ጉዳይና የቁጥጥር ኦፊሰር ማቴ ሃሪሰን ሃርቬይ ተናግረዋል፡፡ ተቋሙ ጨረታውን ማሸነፉን […]

ዩጋንዳ የኮቪድ-19 መከላከያ ያልተከተቡ ሰዎችን በገንዘብና በእስራት መቅጣት የሚያስችል ህግ አረቀቀች::

አዲስ አበበ፣ የካቲት 16፣ 2014 ዩጋንዳ የኮቪድ-19 መከላከያ ያልተከተቡ ሰዎችን በገንዘብና በእስራት መቅጣት የሚያስችል ህግ አረቀቀች፡፡ ለሀገሪቱ ፓርላማ የቀረበው ይህ የህግ ረቂቅ ክትባት ለመውሰድ አሻፈረኝ በሚሉ ዜጎች ላይ 1 ሺህ 139 ዶላር ወይም 4 ሚሊዮን የሀገሪቱን ገንዘብ የሚያስቀጣ ሲሆን የሥድስት ወር እስራትንም ያካትታል፡፡ የጤና ሚኒስትሯ ዶክተር ጄን ሩት አሴንግ ረቂቅ ህጉን አስመልክተው በሰጡት ማብራሪያ ዜጎችን […]

የአድዋን ታሪክ በሚገባ በመለየት አሁን ላለንበት ችግር መፍቻ ቁልፍ ማድረግ ይገባል ሲሉ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ባህል ኪነ ጥበባትና ቱሪዝም ቢሮ ሃላፊ ዶ/ር ሂሩት ካሳው ገለጹ።

አዲስ አበባ፣ የካቲት 21፣ 2014 የአድዋን ታሪክ በሚገባ በመለየት አሁን ላለንበት ችግር መፍቻ ቁልፍ ማድረግ ይገባል ሲሉ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ባህል ኪነ ጥበባትና ቱሪዝም ቢሮ ሃላፊ ዶ/ር ሂሩት ካሳው ገለጹ። ለ126ኛ ጊዜ “አድዋን ለኢትዮጵያውያን ኅብረት፣ ለአፍሪካ የነፃነት ጮራ” በሚል መሪ ሃሳብ የሚከበረውን የአድዋ ድል በዓል አስመልክቶ የውይይት መድረክ ተካሄዷል፡፡ የቢሮ ኃላፊዋ በመድረኩ ላይ እንደገለጹት፣ […]

አዲስ አበባ፣ የካቲት 21፣ 2014 በሶማሌ ክልል በድርቅ ለተጎዱ ወገኖች 31 ሚሊዮን ብር የሚገመት ድጋፍ ተበረከተ::

አዲስ አበባ፣ የካቲት 21፣ 2014 በሶማሌ ክልል በድርቅ ለተጎዱ ወገኖች 31 ሚሊዮን ብር የሚገመት ድጋፍ ተበረከተ በሶማሌ ክልል በድርቅ በተጎዱ አካባቢዎች ለሚገኙ ጤና ተቋማት አገልግሎት የሚውል 31 ሚሊዮን ብር የሚገመት የተለያዩ መድሃኒቶች፣ የተመጣጠነ ምግብ እና የህክምና ቁሳቁሶች ድጋፍ ተደርጓል። በጤና ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ ሰሀረላ አብዱላሂ የተመራ ከጤና ሚኒስቴር፣ የኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት እና የኢትዮጵያ መድሃኒት […]