loading
አትሌት ፈይሳ ሌሊሳ ወደ ሀገር ቤት ሊገባ ነዉ፡፡

ቪኦኤ እንደዘገበዉ አትሌት ፈይሳ በቅርቡ ቤተሰቡን ይዞ ወደ ሀገር ቤትለመመለስ ወስኗል፡፡ ከቀናት በፊት የኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ኮሚቴና የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌደሬሽን በጋራ ባወጡት መግለጫ አትሌት ፈይሳ ሌሊሳን ወደ ሀገሩ እንዲመለስ መጋበዛቸዉ ይታወሳል፡፡በወቅቱም ለአትሌቱ የጀግና አቀባባል እንደሚያደርጉ ገልጸዋል፡፡

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በ2010 በጀት ዓመት ካቀድኩት ማሳካት የቻልኩት 49.5 በመቶ ብቻ ነዉ አለ፡፡

አገልግሎቱ ለ468 ሺህ ደንበኞች ኤሌክትሪክ ለማዳረስ አቅዶ ለ231 ሺህ 781 ደንበኞች ብቻ ነው ኤሌክትሪክ ማድረስ የቻልኩት ብሏል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የ2010 በጀት ዓመት የዕቅድ አፈጻጸም እና የ2011 በጀት አመት ዕቅድን ዛሬ ባቀረበበት ወቅት የተቋሙ ምክትል ስራ አስፈጻሚና የአዲስ አበባ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ኃላፊ አቶ ብዙወርቅ ደምሰዉ ኃይል በማምረት ደረጃ ሰፊ ስራዎችን ማከናወን ቢችልም ለተጠቃሚዎች በማዳረስ ረገድ […]

የአማራ ክልል ልዑክ በአስመራ ከአማራ ዲሞክራሲያዊ ኃይል ንቅናቄ ጋር ምክክር ጀመረ፡፡

አዴኃንና የአማራ ክልል መንግስት የአማራን ህዝብ ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ማረጋገጥ የዉይይታቸዉ ሀሳብ ነዉ፡፡ አዴኃን ወደ ሀገሩ ገብቶ በሰላም እንዲንቀሳቀስና ጥሩ አጋር ሆኖ እንዲሰራ የክልሉ መንግስት ድጋፍ እንደሚያደርግለትም ገልጧል ልዑኩ፡፡ የልኡኩ አባል የአማራ ክልል መንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ዋና ዳይሬክተር አቶ ንጉሱ ጥላሁን የኤርትራ መንግስት ጉዳዩ እልባት እንዲያገኝ ያሳየውን አጋርነት ማድነቃቸዉን የአማራ መገናኛ ብዙሃን ዘግቧል፡፡ የኤርትራ ውጭ […]

በምስራቅ ጎጃም በደረሰ የመሬት መንሸራተት አደጋ የ8 ሰዎች ህይወት አለፈ፡፡

በምስራቅ ጎጃም ዞን ጎንቻ ሲሶ እነሴ ወረዳ በተከሰተ የመሬት መንሸራተት አደጋ የ8 ሰዎች ህይወት ማለፉን ፋና ዘግቧል። ጎንቻ ሲሶ እነሴ ወረዳ የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት እንዳስታወቀው፥ አደጋው የደረሰው ነሃሴ ነሀሴ 8 ቀን 2010 ዓ.ም ከሌሊቱ 7 ሰዓት አካባቢ ነው። በመሬት መንሸራተት አደጋውም የ8 ሰዎች ህይወት ሲያልፍ ስድስቱ የአንድ ቤተሰብ አባላት ሲሆኑ፥ ሁለቱ ደግሞ ስራ […]

የኦሮሚያ የከተሞች ስራ ዕድል ፈጠራና ምግብ ዋስትና ኤጀንሲ በ2011 በጀት ዓመት ስራ አጥና በግል ስራ ላይ ለተሰማሩ ወጣቶች 3.283 ቢሊዮን ብር ለመስጠት አዘጋጅቻለሁ አለ፡፡

በዚህም 1.1 ሚሊዮን ወጣቶችን በ90 ማህበራት ለማደራጀት ተወስኗል፡፡ ከነዚህ መካከል 64 ሺህ የሚሆኑት ከመንግስት ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የሚመረቁ ናቸው፡፡ ለመፍጠር በተዘጋጀው የስራ ዕድል 52205 ሄክታር የከተማና የገጠር መሬት ተዘጋጅቷል፡፡ እንዲሁም 4648 አዳዲስ ሼዶች የሚገነቡ ይሆናል፡፡ የክልሉ ፕሬዝዳንት አቶ ለማ መገርሳ በወቅቱ እንዳሳወቁት ወጣቶች የተፈጠረላቸውን የስራ ዕድል ብቻ ሳይሆን በሃገር የኢኮኖሚ እድገት ላይ ተፅዕኖ ሊያሳድሩ እንደሚችሉ […]

የመጀመሪያው የቴክኖሎጂ ከተማ በባህር ዳር ሊገነባ ነው፡፡

የሳይንስና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ከአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስትና ከአሜሪካው ሀብ ሲቲ ላይቭ ፕሮጀክት ጋር በመተባበር በባህር ዳር ከተማ የመጀመሪያውን የቴክኖሎጂ ከተማ (Technology Hub City) ለመገንባት በሚቻልበት ሁኔታ ላይ የምክክር መድረክ አዘጋጅቷል፡፡ የምክክር መድረኩ በሳይንስና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ነገ ይካሄዳል፡፡ ምክክሩ Ethiopia is the Real WAKANDA በሚል ርዕስ እንደሚካሄድ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር በገፁ ፅፏል፡፡ የቴክኖሎጂ ከተማው በከፍተኛ ወጪ […]

ለስደተኞች ስራ በማትሰጠው ለንደን ወጣቱ ሲቪውን ይዞ ጎዳና ላይ ለመቆም ተገዷል ፡፡

ሞሀመድ ኤልባራዲ ይባላል፡፡ የ22 ዓመት ወጣት ነው፡፡ ከሊቢያ ተሰዶ መኖሪያውን ለንደን ያደረገው ኤልባራዲ ከለንደን ዩንቨርሲቲ ኮሌጅ በኤሮስፔስ ሳይንስ በማስተርስ ዲግሪ ተመርቋል፡፡ ሆኖም ከ70 በላይ በሚሆኑ ቀጣሪ ድርጅቶች ውስጥ የስራ ማመልከቻ ቢያስገባም አንዳቸውም ምላሽ አልሰጡትም፡፡ በዚህ ሁኔታ የተማረረው ኤልባራዲ ታዲያ በመጨረሻ አንድ ሀሳብ መጣለት፡፡ ስራ እንደሚፈልግ የሚጠቁም ማስታወቂያ ይዞ ሰው በሚበዛበት አካባቢ መቆም፡፡ እናም ይህ ወጣት […]

በህንድ በተከሰተ የጎርፍ አደጋ ከመቶ በላይ ሰዎች ሲሞቱ በሺዎች ሚቆጠሩት ደግሞ ከቤት ንብረታቸው ተፈናቅለዋል ፡፡

በህንድ በተከሰተ የጎርፍ አደጋ ከመቶ በላይ ሰዎች ሲሞቱ በሺዎች ሚቆጠሩት ደግሞ ከቤት ንብረታቸው ተፈናቅለዋል ፡፡ ቢቢሲ እንደዘገበው የህንዷ ኬራላ ግዛት ህንድን በክፍለ ዘመኑ ካጋጠማት አስከፊውን የጎርፍ አደጋ አስተናግዳለች፡፡ የግዛቷ ባለስልጣናት እንደተናገሩት በአደጋው ሳቢያ 164 ሰዎች ህይወታቸው አልፏል፡፡ ከሟቾቹ በተጨማሪም ቁጥራቸው ወደ 23 ሺህ የሚጠጋ ነዋሪዎች ቤት አልባ ሆነዋል፡፡ ባለስልጣናቱ ነዋሪዎቹ በፍጥነት የአደጋውን አካባቢ ለቀው እንዲወጡም […]

አዲስ አመትን ለማክበር ወደ አዲስ አበባ እየገቡ ያሉ በውጪ ሀገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን በበጎ ፍቃድ አገልግሎት ለመሳተፍ ጥያቄ ማቅረባቸዉን የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ ኢንጂነር ታከለ ኡማ በትዊተር ገጻቸዉ አስታዉቀዋል፡፡

አዲስ አመትን ለማክበር ወደ አዲስ አበባ እየገቡ ያሉ በውጪ ሀገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን በበጎ ፍቃድ አገልግሎት ለመሳተፍ ጥያቄ ማቅረባቸዉን የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ ኢንጂነር ታከለ ኡማ በትዊተር ገጻቸዉ አስታዉቀዋል፡፡ ኢንጂነር ታከለ ዲያስፖራውን በቀጣይም በከተማዋ ልማት ላይ እንዲሳተፍ ጥሪያችንን እናቀርባለን ብለዋል