loading
የአልሲሲ የጂቡቲ ጉብኝትና አጋር የማብዛት ስትራቴጂ::

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 19፣ 2013ፕሬዚዳንት አብደልፈታህ አልሲሲ ከፕሬዚዳንት እስማኤል ኦማር ጌሌ ጋር በሁለትዮሽ ጉዳይ ለመምከር ወደ ጂቡቲ አቅንተዋል፡፡ ኢጂፕት ቱደይ በዘገባው እንዳስነበበው አልሲሲ ጂቡቲን ሲጎበኙ በግብፅ ፕሬዚዳንቶች ታሪክ የመጀመሪያው ሰው ሆነው ተመዝግበዋል፡፡ የግብፅ ፕሬዚዳንት ፅህፈት ቤት ቃል አቀባይ ባሳም ራዲ በሰጡት መግለጫ የአልሲሲ ጉብኝት ዋነኛ ዓላማ በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን ግንኙነትነ ማጠናከር ላይ የሚያጠነጥን […]

በናይጄሪያ የኮሌራ ወረርሽኝ ስጋት::

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 19፣ 2013  በናይጄሪያ የኮሌራ በሽታ መከሰቱን ተከትሎ 20 ሰዎች መሞታቸው ተሰማ በሰሜናዊው የሀገሪቱ ክፍል በተከሰተ የኮሌራ በሽታ ባለፉት ሁለት ሳምንታት ውስጥ የ20 ሰዎች ህዎት ሲያልፍ ከ300 በላይ ሰዎች ደግሞ ሆስፒታል ገብተዋል ተብሏል፡፡ ባውቺ በተባለችው ግዛት የተከሰተው የኮሌራ በሽታ በዘጠኝ ወረዳዎች ላይ ከፍተኛ መስፋፋት ማሳየቱን የግዛቷ ጤና ኮሚሽነር ሞሃመድ ሚጎሮ ገልፀዋል፡፡ አፍሪካ […]

በቡርኪናፋሶ በተፈጸመ የታጣቂዎች ጥቃት ብዙዎች ህይወታቸዉ አለፈ::

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 30፣ 2013  በቡርኪናፋሶ በተፈጸመ የታጣቂዎች ጥቃት የሟች ቁጥር ከ130 በላይ መድረሱ ተሰማ  መረጋጋት በተሳነው ምእራባዊ የሀገሪቱ ክፍል የ132 ሰዎችን ህይዎት የቀጠፈውን የታጣቂዎች ጥቃት የተባበሩት መንግስታ ድርጅት በፅኑ አውግዞታል፡፡ ታጣቂቂዎች ድንገተኛ ተኩስ በመክፈት ጥቃቱን ያደረሱት ዮጋ ተብላ በምትጠራው ግዛት በምትገኘውና ከኒጀር ጋር በምትዋሰነው የሶልሃን መንደር ነው፡፡ የሀገሪቱ መንግስት ቃል አቀባይ ፅህፈት ቤት […]

አፍሪካዊ ችግሮች አፍሪካዊ መፍትሄ ማግኘት እንሚገባው ኬኒያ አሳሰበች::

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 1፣ 2013 የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን ጋረ ከኬንያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ሪይቸል ኦማሞ ጋር በሁለትዮሽ እና በወቅታዊ ሀገራዊ ሁኔታዎችን በተመለከተ በጽሕፈት ቤታቸው ውይይት አድርገዋል። አምባሳደር ሬድዋን በቀጣዩ ሀገራዊ ምርጫ፣ በኢትዮ-ሱዳን የድንበር ጉዳይ፣ በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የሦስትዮሽ ድርድር እንዲሁም የትግራይ ክልል ወቅታዊ ሁኔታዎችን በተመለከተ ለአምባሳደሯ ማብራሪያ ሰጥተዋል። […]

በሱዳን የተከሰተው የነዳጅ ዋጋ ጭማሪ የህዝባዊ አመፅ ስጋት ፈጥሯል ::

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 3፣ 2013 በሱዳን የተከሰተው የነዳጅ ዋጋ ጭማሪ የህዝባዊ አመፅ ስጋት ፈጥሯል ::ሱዳን ድጎማ ማንሳቷን ተከትሎ የነዳጅ ዋጋ በሊትር የ140 የሱዳን ፓውንድ ጭማሪ ማሳየቱ ተሰማ፡፡ ካርቱም የዓለም አቀፉን የገንዘብ ድርጅት ምክር ተቀብላ የነዳጅ ድጎማ ማንሳቷ ያስከተለው የዋጋ ንረት ህዝባዊ ከባድ አመፅ እንዳይቀሰቀስ ስጋት ላይ ጥሏታል ነው የተባለው፡፡ በዚህም የተነሳ ለአልበሽር ከመንበራቸው መወገድ […]

በሀገራት የውስጥ ጉዳይ ጣልቃ መግባት አግባብ አይደለም-¬ቻይና፡፡

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 11፣ 2013 ኢትዮጵያ ልዩነቶችን በውይይት ለመፍታት የውጭ ጣልቃ ገብነት እንደማያስፈልጋት ቻይና ገለጸች፡፡ አምባሳደር መለስ ዓለም በኬንያ ከቻይና አምባሳደር ዦ ፒንጂያን ጋር በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ውይይት አድርገዋል። በዚሁ ወቅት አምባሳደሩ በአገሮች የውስጥ ጉዳይ የሚደረግ ጣልቃ ገብነት ቻይና እንደምትቃወም ተናግረዋል። የውስጥ ጉዳይ የየአገራቱ ኃላፊነት በመሆኑ ሌሎች አገሮች በተናጥል ጣልቃ መግባት እንደሌለባቸው አምባሳደር ፒንጂያን […]

ዛምቢያ የነፃነት አባቷን በሞት ተነጠቀች::

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 11፣ 2013 በዛምቢያዊያን ዘንድ የነፃነት አባት በመባል የሚታወቁት የቀድሞው ፕሬዚዳንት ኬኔት ካውንዳ በ97 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ፡፡ካውንዳ ከቀናት በፊት ሉሳካ ወደሚገኘው ወታደራዊ ሆስፒታል ገብተው ህክምናቸውን ቢከታተሉም ሀኪሞቻቸው ህይዎታቸውን ማትረፍ አልተቻላቸውም፡፡ የሀገሪቱ ባለሥልጣናት በሰጡት መግለጫ በሽታቸው ከሳንባ ምች ጋር የተገናኘ እንደሆነ ይፋ አድርገዋል፡፡ ረዳታቸው ሮድሪክ ንጎሎ ለአጃንስ ፍራንስ ፕሬስ በሰጡት ቃለ […]

ሱዳን የሽግግር መንግስትና በተቃዋሚ ሃይሎች የተጀመረው የሰላም ድርድር አሁንም እክል ገጥሞታል ተባለ::

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 21፣ 2013 በ እስካሁን በተደረጉ ውይይቶች በፖለቲካና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች ዙሪያ መግባባቶች ቢኖሩም በማእከላዊ መንግስትና በክልሎች መካከል በሚኖረው የሥልጣን ውክልና መስማማት አልተቻላቸውም፡፡ አጃንስ ፍራንስ ፕሬስ እንደዘገበው የሱዳን ህዝቦች ነፃነት ንቅናቄን ወክለው የሚደራደሩት አማር አሞን ዋና ዋና ሀገራዊ ስምምነቶች ወደፊት በህዝበ ውሳኔ እንዲረጋገጡ እንፈልጋለን ብለዋል፡፡ በተለይ በሁለቱ ሃይሎች መካከል አለመግባባት እንዲካረር ያደረገው ዋነኛ […]

አዲሱ የኮቪድ -19 ዝርያ ደቡብ አፍሪካን እያመሳት ነዉ ፡፡

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 21፣ 2013 ዴልታ የተሰኘው አዲስ የኮሮና ቫይረስ ዝርያ ደቡብ አፍሪካን ክፉኛ እየጎዳት ነዉ ተባለ አዲሱ የኮሮና ቫይረስ ዝርያ መጀመሪያ በህንድ የተገኘ ሲሆን፤ በደቡብ አፍሪካም የዚሁ የኮሮና ቫይረስ ዝርያ አሳሳቢነት ከፍ እያለ በመምጣቱ አዲስ የእንቅስቃሴ ገደብ ለመጣል ተገዳለች፡፡ ሀገሪቱንም በጥር ወር ወደነበረችበት አሳሳቢ ሁኔታ እየመለሳት የሚገኘው ይህ ቫይረስ ባለፉት ሁለት ቀናት ብቻ […]

ቶጎ በምዕራብ አፍሪካ ግዙፍ የተባለውን የፀሃይ ሃይል ማመንጫ ይፋ አደረገች::

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 22፣ 2013 ከዋና ከተማዋ ቶጎ በደቡባዊ አቅጣጫ 250 ኪሎ ሜትር ላይ የሚገኝው ይህን ፕሮጀክት የሀገሪቱን የኤሌክትሪክ ችግር ይቀርፋል ተብሎ ታምኖበታል፡፡ ፕሮጀክቱ 158 ሺህ የሚሆኑ አባወራዎችን ተጠቃሚ የሚያደርግ ሲሆን ከአንድ ሚሊዮን በላይ ሰዎችን በቀጣይ ለማዳረስ ዕቅድ ተይዞለታል ነው የተባለው፡፡ በአቡዳቢው ልኡል ሼክ ሙሃመድ ቢን ዛይድ የተሰየመው ይህ ፕሮጀከት 64 ነጥብ 7 ሚሊዮን […]