loading
የፖለቲካ ፓርቲዎች በመገናኛ ብዙኃን የምርጫ ቅስቀሳ ማድረግ ሊጀምሩ ነው::

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 29፣ 2013 የፖለቲካ ፓርቲዎች በመገናኛ ብዙኃን የምርጫ ቅስቀሳ ማድረግ ሊጀምሩ ነው::ለ6ኛው አገራዊ ምርጫ የሚሳተፉ የፖለቲካ ፓርቲዎች የምርጫ ቅስቀሳ ከነገ ጀምሮ በመገናኛ ብዙኃንማድረግ እንደሚችሉ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አስታውቋል፡፡የፖለቲካ ፓርቲዎች ለምረጡኝ ዘመቻቸው የሚጠቀሙበት ነፃ የአየር ሰዓት እና የጋዜጣ አምድ እጣ ድልድል መርሐ-ግብር ተከናውኗል፡፡ ድልድሉ 25 በመቶ ለፓርቲዎች በእኩል ክፍፍል የሚሰጥ ሲሆን፣ በስራ ላይ ባሉ […]

በአለም የመጀመሪያውን ከመጠን ያለፈ ውፍረትን ለመቆጣጠር የሚረዳ በጨጓራ ላይ የሚታሰር ቀለበት የፈለሰፉት ፕ/ር ምትኩ በላቸው ከዚህ አለም በሞት ተለዩ::

በአለም የመጀመሪያውን ከመጠን ያለፈ ውፍረትን ለመቆጣጠር የሚረዳ በጨጓራ ላይ የሚታሰር ቀለበት የፈለሰፉት ፕ/ር ምትኩ በላቸው ከዚህ አለም በሞት ተለዩ::ታዋቂው የቀዶ ህክምና እስፔሻሊስት ፕሮፌሰር ምትኩ በላቸው በምእራብ ሸዋ ወንጪ የተወለዱ ሲሆን እድሚያቸዉ 12 አመት ሲሞላ ወደ አዲስ አበባ በመምጣት ከመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤት እስከ ከፍተኛ ትምህርት ተቋም ትምህርታቸዉን ተከታትለዋል፡፡ ፕ/ር ምትኩ ትምህርታቸዉን ሲከታተሉ ከነበረበት የአሁኑ አዲስ […]

አዲስ አበባን ለነዋሪዎቿ ምቹ ከተማ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ምክትል ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ::

አዲስ አበባ፣  ሚያዚያ ፡ 04፣ 2013 አዲስ አበባን ለነዋሪዎቿ ምቹ ከተማ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ምክትል ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ:: አዲስ አበባን ለነዋሪዎቿ ሁሉ ምቹ ከተማ ለማድረግ የተለያዩ የልማት ተግባራት ተጠናክረው መቀጠላቸውን የከተማ አስተዳደሩ ምክትል ከንቲባ አዳነች አቤቤ ተናገሩ። የከተማ አስተዳደሩ የአርሶ አደር መንደሮችን ተዳራሽ ማድረግ የሚያስችሉ የመንገድ ስራፕሮጀክቶችን አስጀምሯል። የከተማ መስተዳደሩ ምክትል ከንቲባ አዳነች አቤቤ […]

ዜጎች የመምረጥ ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን በመጠቀም ንቁ ተሳትፎ እንዲያደርጉ ይጠበቃል አሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ፡፡

አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 6፣ 2013 ዜጎች የመምረጥ ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን በመጠቀም ንቁ ተሳትፎ እንዲያደርጉ እንደሚጠበቅ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ገለጹ፡፡ጠቅላይ ሚኒስትሩ 6ኛው ብሔራዊ ምርጫ ሊከናወን ጥቂት ሳምንታት ብቻ ቀርተውታል ያሉ ሲሆን፤ በሕገ መንግሥቱን አንቀጽ 38 ሁሉም ኢትዮጵያዊ የመምረጥና የመመረጥ መብት እንደሚደነግግ ገልጸዋል። የሀገራችንን የነገ ዴሞክራሲ ለመወሰን፣ ዛሬ የመራጮች ምዝገባ መታወቂያ ካርድ እናውጣ ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ካርድ […]

ዶክተር ፋና ሀጎስ የመቐለ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ሆነው ተሾሙ::

አዲስ አበባ ፣ ሚያዝያ 7 ፣ 2013  ዶክተር ፋና ሀጎስ ብርሃኔ የመቐለ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ሆነው ተሾመዋል። ዶክተር ፋና ሀጎስ ብርሃኔ የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በህግ ትምህርት የተቀበሉ ሲሆን ሁለተኛና ሶስተኛ ዲግሪያቸውን በደቡብ አፍሪካ ዩኒቨርሲቲ ኦፍ ፍሪስቴትና ዋርዊክ ዩኒቨርሲቲ ተምረዋል፡፡ ትምህርታቸውን በመቀጠልም ኬኒያ ናይሮቢ ከሚገኘው የአፍሪካ ሳይንስ አካዳሚ ፖስት ዶክትሬት አግኝተዋል፡፡በትግራይ ክልል ፍትህ ቢሮ ዐቃቤ […]

የአውሮፓ ህብረት በኢትዮጵያ ለሰብአዊ ድጋፍ ከ53 ሚሊየን ዩሮ በላይ ድጋፍ አደረገ፡፡

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 11፣ 2013 የአውሮፓ ህብረት በትግራይና ሌሎች የሃገሪቱ አካባቢዎች የሰብአዊ ድጋፍ ለሚያስፈልጋቸው ዜጎች 53 ነጥብ 7 ሚሊየን ዩሮ ድጋፍ አድርጓል፡፡ድጋፉ በትግራይ ክልል ሰብአዊ ድጋፍ የሚያስፈልጋቸው ወገኖችን ጨምሮ በግጭትና በአየር ንብረት ለተጎዱ ወገኖች የሚውል እንደሆነ ነው የተገለጸው፡፡ የህብረቱ የቀውስ አመራር ኮሚሽነር ጃኔዝ ሌናርቺቺ ድጋፉ ትግራይ ክልልን ጨምሮ በተለያዩ አካባቢዎች እርዳታ ለሚያስፈልጋቸው ሰዎች ሰብአዊ ድጋፍ […]

በግድቡ ዙያሪያ የማይናወጠው የኢትዮጵያ አቋም፡፡

አዲስ አበባ ፣ ሚያዝያ 12 ፣ 2013 ግብፅና ሱዳን የአፍሪካ ህብረትን የአደራዳሪነት ሚና ተቀብለው ወደ ሶስትዮሽ ድርድሩ እንዲመለሱ ኢትዮጵያ ጥሪ አቀረበች፡፡ ኢትዮጵያ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በኩል ለፀጥታው ምክር ቤት በፃችፈው ደብዳቤ በአፍሪካ ህብረት የሚመራው ሂደት የፀጥታው ምክር ቤትን መርሆዎች መሠረት ያደረገና ለአፍሪካዊ ችግሮች አፍሪካዊ መፍትሄዎችን የሚያፈላልግ መሆኑን ገልፃለች፡፡ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትርና ምክትል ጠቀቅላይ ሚኒስትሩ አቶ […]

የአብን የሰላማዊ ትግል ጥሪ::

አዲስ አበባ ፣ ሚያዝያ 12 ፣ 2013 አብን በአማራ ሕዝብ ላይ ለተፈፀሙት ተደጋጋሚ የዘር ማጥፋት ወንጀሎች ብሔራዊ እውቅና እንዲሰጥ ፀየቀ ፡፡ ፓርቲው ባወጣው መግለጫ አማራ በገዛ ሀገሩ እንደጠላት መታየቱ ማክተም እንዳለበትና ለደረሰበት በደል ይቅርታ እንዲጠየቅም አሳስቧል፡፡ በክልሉ ህዝብ ላይ ለዓመታት የቀጠለው የጅምላና የተናጥል ግድያ እንዲሁም ጅምላ ማፈናቀልን ለማስቆም የፌደራሉም ሆነ የክልሉ መንግስት ምንም አይነት ፍላጎት […]

የኢሕአፓ ኢትየዮጵያን የአረብሊግና የኔቶ አባል የማድረግ ፍላጎት::

አዲስ አበባ ፣ ሚያዝያ 12 ፣ 2013  አርትስ ቲቪ ያዘጋጀው የመጀመሪያ ዙር የፓለቲካ ፓርቲዎች ክርክር ተካሂዷል፡፡ በክርክሩ ላይም የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ፣ ህብር ኢትዮጵያ እና የኢትዮጵያ ህዝቦች አብዮታዊ ፓርቲ ኢህአፓ ተሳትፈዋል፡፡ ሶስቱ ፓሪቲዎች በስድሰተኛው ሀገራዊ ምርጫ አሸንፈው ስልጣን ቢይዙ ሊተገብሩ ባዘጋጁት የውጭ ጉዳይ እና የደህንነት ፖሊሲ ላይ ክርክር አድርገዋል፡፡ ኢዜማን ወክለው በክርክሩ የቀረቡት አቶ ግርማ […]

ጠ/ሚ አብይ በግድቡ ላይ ባሉ አለመግባባቶችና የውይይት መጓተቶች ላይ ስብስባ እንዲጠራ ጠየቁ::

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 13፣ 2013 ጠ/ሚ አብይ በግድቡ ላይ ባሉ አለመግባባቶችና የውይይት መጓተቶች ላይ ስብስባ እንዲጠራ ጠየቁ:: ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ለሱዳኑ ጠቅላይ ሚኒስትር አብደላ ሃምዶክ በሚያዝያ ወር መጀመሪያ ላይ ለጻፉት ደብዳቤ ምላሽ የሰጡ ሲሆን፥ ኢትዮጵያም የወቅቱ የአፍሪካ ህብረት ሊቀ መንበርና ለዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ፕሬዚዳንት ፌሊክስ ሺሴኬዲ ከግድቡ ጋር በተያያዘ ባሉ መጓተቶች ላይ ስብሰባ እንዲጠሪ […]