loading
በኢትዮጵያ ባለፉት 24 ሰዓታት 11 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ ምክንያት ህይወታቸው አለፈ፡፡

አዲስ አበባ፣ ነሃሴ 11፣2013 በኢትዮጵያ ባለፉት 24 ሰዓታት 11 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ ምክንያት ህይወታቸው አለፈ፡፡ የጤና ሚኒስቴር በ24 ሰዓቱ የኮቪድ-19 ሪፖርት መረጃው ላይ እንዳስታወቀው ፤ በቫይረሱ ምክንያት 11 ሰዎች ህይወታቸው አልፏል፡፡ እስካሁንም በሀገሪቱ በኮሮና ምክንያት ህይወታቸውን ያጡ ሰዎች ቁጥርም 4 ሺህ 4 መቶ 89 ደርሷል፡፡ በ24 ሰዓታት ዉስጥ 5ሺህ 1 መቶ 73 ሰዎች ላብራቶሪ ምርመራ […]

ጠ/ሚ ዐቢይ በወታደራዊ ማሰልጠኛዎች ዝግጅቶችን ላቀረቡ የኪነጥበብ ባለሙያዎች ምስጋና አቀረቡ::

አዲስ አበባ፣ ነሃሴ 11፣2013 ጠ/ሚ ዐቢይ በወታደራዊ ማሰልጠኛዎች ዝግጅቶችን ላቀረቡ የኪነጥበብ ባለሙያዎች ምስጋና አቀረቡ::ኢትዮጵያን ለማዳን እዘምታለሁ መቼም፣ የትም፣ በምንም በሚል መሪ ቃል፣ የብሔራዊ ቴአትር፣ ኦሮሞ የባህል ማዕከልና የአዲስ አበባ ቴአትር ቤቶች የኪነ ጥበብ ባለሞያዎች በወታደራዊ ማሠልጠኛዎች ተገኝተው ዝግጅቶችን አቅርበዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በትዊተር ገጻቸው ላይ ባሰፈሩት መልዕክት÷ኪነ ጥበብ ምንጊዜም ከኢትዮጵያ ጀግንነት ጋር ናት ብለዋል፡፡ በዚህም ዝግጅቶቹን […]

በሳዑዲ አረቢያ እስርቤቶች የሚገኙ ኢትጵያዊያን ወደ ሀገራቸው ሊመለሱ ነው፡፡

አዲስ አበባ፣ ነሃሴ 12፣2013 በሳዑዲ አረቢያ የተለያዩ ማቆያ ማእከላትና እስር ቤቶች የሚገኙ ኢትዮጵያዊያን ከዚህ ሳምንት ጀምሮ ወደ ሀገራቸው እንደሚመለሱ ተገለፀ፡፡ የዉጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ጽ/ቤት በሪያድ የሚገኘነውን የኢትዮጵያ ኤምባሲን ጠቅሶ በፌስቡክ ገጹ እንዳሰፈረው፤ የኢትዮጵያ መንግስት ከሳዑዲ አረቢያ መንግስት ጋር በመቀናጀት በሳምንት ሶሶት በረራዎችን በማድርግ በሳዑዲ አረቢያ የተለያዩ ማቆያ ማዕከላትና እስር ቤቶች የሚገኙ ዜጎችን ከዚህ […]

51 ሺህ 89 ኢትዮጵያዊያን ከሀገር ወጥተው የት እንዳሉ አይታወቅም::

አዲስ አበባ፣ ነሃሴ 12፣2013 ከሀገር ውጪ ፈልሰው አድራሻቸው ያልታወቁ 51 ሺ 89 ዜጎች መኖራቸውን የማዕከላዊ ስታቲስቲክስ ኤጀንሲ አስታወቀ፡፡ ኤጀንሲው የአለማቀፍ ፍልሰት ድርጅት እና ዳኒሽ ከተባለ ግብርሰናይ ድርጅት ጋር በመተበባር ባስጠናው ጥናት 51 ሺ 89 ኢትዮጵያዊያን ከሀገር እንደወጡ የት እንዳሉ እንዳልታወቀ ደርሼበታለሁ ብሏል፡፡ ከ41 ሺህ በላይ ቤተሰቦች ለተካተቱበት ለዚህ ጥናት የኢትዮጵያ መንግስት 36 ሚሊዮን ብር ያወጣበት […]

የቱርክ የፊልም ኢንዱስትሪም የህዝብ ለህዝብ ግንኙነትን እያጠናከረ ነው-ጠ/ሚ ዐቢይ::

አዲስ አበባ፣ ነሃሴ 13፣2013 የለውጥ ሂደቱ ከጀመረበት ጊዜ አንስቶ ኢትዮጵያና ቱርክ ግንኙነታቸውን ለማጠናከር በጋራ እየሰሩ ነው:: ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ገለጹ፡፡ ኢትዮጵያና ቱርክ የሁለትዮሽ ግንኙነታቸውን ማጠናከር የሚያስችሉ ተጨማሪ  ስምምነቶችን ተፈራርመዋል። በቱርክ የስራ ጉብኝት እያደረጉ የሚገኙት ጠቅላይ ሚኒስትር አቢይ አህመድ ከቱርኩ ፕሬዚዳንት ሬሲፕ ጣይብ ኤርዶጋን ጋር በመሆን መግለጫ ሰጥተዋል። ፕሬዚዳንት ኤርዶጋን በመግለጫቸው ሁለቱ አገሮች ያላቸው ግንኙነት ወንድማማችነት ነው ብለዋል፡፡ በጠቅላይ ሚኒስትሩ በሚመራው […]

ህወሓትን ሲደግፉ የነበሩ ግለሰቦችን ለህግ ለማቅረብ ከኢንተርፖል ጋር እየሰራን ነዉ-ፌደራል ፖሊስ::

አዲስ አበባ፣ ነሃሴ 13፣2013  ለአሸባሪው ህወሓት የኢኮኖሚ ምንጭ ሆነው ሲያገለግሉ የቆዩ 117 የንግድ ድርጅቶች እና መኖሪያ ቤቶች ላይ ህጋዊ እርምጃ መውሰዱን የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ። ኮሚሽኑ ህገወጥ ምንዛሪን አስመልክቶ ለአርትስ በላከው መግለጫ እንዳስታወቀው ባካሄደው የተቀናጀ ኦፕሬሽን ለሽብር ቡድኑ የኢኮኖሚ ምንጭ በመሆን ሲያገለግሉ የነበሩ የንግድ ድርጅቶች እና መኖሪያቤቶች ላይ ህጋዊ እርምጃ በመውሰድ የአሸባሪው ቡድን የፋይናንስ ምንጭ […]

በዋሽንግተን ዲሲና አካባቢው የሚገኙ ታዳጊዎች የቡሄ በዓልን በማስመልከት ለህዳሴ ግድብ ገንዘብ አሰባሰቡ፡፡

አዲስ አበባ፣ ነሃሴ 13፣2013  በዋሽንግተን ዲሲና አካባቢው የሚገኙ ታዳጊ ኢትዮጵያዊያን የቡሄ በዓልን በማስመልከት ለታላቁ ህዳሴ ግድብ የገቢ ማሰባሰቢያ ፕሮግራም አካሄዱ በፕሮግራሙ ላይም በቡሄ ጭፈራ የታጀቡ መልዕክቶችን አስተላልፈዋል፡፡ ታዳጊዎቹ ካስተላለፏቸዉ መልዕክቶች ውስጥ የግድቡ መጠናቀቅ ህጻናትና ታዳጊዎች ትምህርታቸውን በአግባቡ በመከታተል የተሻለ ሕይወት እንዲመሩ ያስችላቸዋል የሚለው ይገኝበታል፡፡ በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው መረጃውን ያጋሩት በአሜሪካ የኢትዮጵያ አምባሳደር ፍፁም አረጋ የሁሉም […]

የትግራይ ህዝብ ኢትዮጵያን የሚያጸኑ እንጂ የሚያፈርሱ ሀይሎች አካል አይደለም፡፡

አዲስ አበባ፣ ነሃሴ 14፣2013 የትግራይ ህዝብ ኢትዮጵያን የሚያጸኑ እንጂ የሚያፈርሱ ሀይሎች አካል አይደለም፡፡ ኢትዮጵያን ለማፍረስ የውስጥም ሆነ የውጭ ሀይሎች ሲንቀሳቀሱ የትግራይ ህዝብ የመጀመሪያ ከለላ መሆኑን የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ዋና ስራ አስፈፃሚ ዶክተር አብርሃም በላይ ገለጹ፡፡ በአዲስ አበባ የሚኖሩ የትግራይ ተወላጆች በቦሌ ክፍለ ከተማ ተገኝተው ደም በመለገስ ለመከላከያ ሰራዊት ያላቸውን ድጋፍ ገልጸዋል። ዶክተር አብርሃም በላይ […]

ከ4 ሚሊዮን 7 መቶ ሺህ ብር በላይ ግምት ያላቸው 6 መቶ 38 ሳጥን ቢራን ከጫኑት ተሽከርካሪዎች ጋር ሰርቀው ሊሰወሩ የነበሩ ተጠርጣሪዎችን መያዛቸውን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታወቀ፡፡

አዲስ አበባ፣ ነሃሴ 14፣2013  ከ4 ሚሊዮን 7 መቶ ሺህ ብር በላይ ግምት ያላቸው 6 መቶ 38 ሳጥን ቢራን ከጫኑት ተሽከርካሪዎች ጋር ሰርቀው ሊሰወሩ የነበሩ ተጠርጣሪዎችን መያዛቸውን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታወቀ፡፡ ተጠርጣሪዎቹ ወንጀሉን የፈፀሙት በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ 5 ልዩ ቦታው አዲሱ ሚካኤል ገነት ህንፃ ተብሎ በሚጠራው የቢጂ. አይ ኢትዮጵያ ምርቶች ወኪል አከፋፋይ አልታድ ኢትዮጵያ […]

ወርቅን በብር ቀይሮ ለማስቀመጥ በሚሰሩ አሻጥሮች አብዛኛው የወርቅ ምርት ባንክ እየገባ አደለም ተባለ።

አዲስ አበባ፣ ነሃሴ 17፣2013  ወርቅን በብር ቀይሮ ለማስቀመጥ በሚሰሩ አሻጥሮች አብዛኛው የወርቅ ምርት ባንክ እየገባ አደለም ተባለ። የማዕድንና ነዳጅ ሚኒስትሩ ኢንጂነር ታከለ ኡማ ይህንን ያሉት ከጋምቤላ ክልል ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎችና ባለድርሻ አካላት ጋር የማዕድን ዘርፉ በሚጠናከርበት ዙሪያ በተወያዩበት ወቅት ነው። ፈቃድ በተሰጣቸው የወርቅ አዘዋዋሪዎች አስፈላጊውን ክትትልና ጥናት በማካሄድ እርምጃ መውስድ እንሚያስፈልግም ነው የገለጹት። በጋምቤላ ክልል […]