loading
በሰኔ 16ቱ የቦንብ ፍንዳታ በተጠረጠሩት ላይ የመጨረሻ የምርመራ የሶስት ቀን ተጨማሪ ጊዜ ተሰጠ::

የቀድሞው የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሸን ምክትል ኮሚሽነር ግርማ ካሳን ጨምሮ በሰኔ 16ቱ የድጋፍ ሰልፍ ላይ ከተከሰተው የቦንብ ፍንዳታ ጋር በተያያዘ የስራ ክፍተት አሳይተዋል ተብለው በተጠረጠሩት ላይ 14 ተጨማሪ የምርመራ ቀናት ተጠይቆ የመጨረሻ የሶስት ቀን ጊዜ ብቻ ተፈቅዷል።

የመንግስታቱ ድርጅት የጸጥታው ምክር ቤት በኤርትራ ጉዳይ ላይ መክሯል፡፡

ኤርትራ ከኢትዮጵያ ለቀረበላት የእርቅ ጥያቄ የሰጠቸው አወንታዊ ምላሽ ለሰላም ያላትን ቁርጠኝነት ያሳያል ነው የተባለው፡፡ ታዲያ ለዚህ የሰላም አጋዥነቷ የተጣለባት ማእቀብ እንዲነሳላት ኢትዮጵያ ለተባበሩት መንግስታ ድርጅት ጥያቄ አቅርባ ነበር፡፡ ሲ ጂ ቲ ኤን እንደዘገበው አሁን ላይ ድርጅቱ የኤርትራ ማእቀብ ይነሳ ወይም አይነሳ በሚለው ሀሳብ ዙሪያ ምክክር አድርጓል፡፡ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስዊድን አምባሳደር ኦልፍ ስኩግ እንዳሉት ኤርትራና […]

ማንነታቸው ያልታወቀ 40 የታጠቁ ወታደሮችን ይዞ ትግራይ ክልል የገባ አንቶኖቭ አውሮፕላን በመቀሌ አሉላ አባ ነጋ አውሮፕላን ማረፊያ ተያዘ።

ማንነታቸው ያልታወቀ 40 የታጠቁ ወታደሮችን ይዞ ትግራይ ክልል የገባ አንቶኖቭ አውሮፕላን በመቀሌ አሉላ አባ ነጋ አውሮፕላን ማረፊያ ተያዘ። ምንጮች ለቢቢሲ እንደገለፁት በአውሮፕላኑ ውስጥ የነበሩት የታጠቁ ወታደሮች ተልዕኮና ማንነታቸው ባይታወቅም ኢትዮጵያዊያን እንደሆኑ ታዉቋል። ከሁለት ቀናት በፊት ከሱዳን በኩል ወደ ኢትዮጵያ እንደገባ የተጠረጠረው አንቶኖቭ አውሮፕላንና አሳፍሯቸው የነበሩት 40 የታጠቁ ወታደሮች በመቀሌው የአሉላ አባ ነጋ አውሮፕላን ማረፊያ መያዛቸውን […]

ተወዳጁ አርቲስት ፍቃዱ ተክለማርያም ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ።

አርቲስት ፍቃዱ ተክለማርያም ከ1948-2010 ከመድረኩ ንጉሳችን ፣ንጉሥ ቴዎድሮስን፣ንጉሥ ኤዲፐስን ፣ንጉሥ ሐምሌትን፣ ንጉሥ አርማህን በህይወት አጣናቸዉ፡ መቃብር ቆፋሪውና የሬሳ ሳጥን ሻጩ፣ እሳት ሲነድ፣ ቤቴ፣ የሠርጉ ዋዜማ፣ ደማችን፣ የሊስትሮ ኦፔራ፣ አቡጊዳ ቀይሶ፣ ባለካባ ባለዳባ፣ መልዕክት ወዛደር፣ ታርቲዩፍ ከተወነባቸው ይገኙበታል፡፡ ኪነ ጠቢቡ ፍቃዱ ተክለማርያም በቴሌቪዥን ከተወናቸው ተውኔቶች መካከልም ያልተከፈለ ዕዳ፣ የአበቅየለሽ ኑዛዜ፣ ባለጉዳይና በሕዝብ ዘንድ አድናቆትን ያተረፉለት ናቸው፡፡ […]

አገሪቱ በአምቡላንስ ቁጥር የዓለም ጤና ድርጅትን መስፈርት አሟልታለች ተባለ፡፡

የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር 746 አምቡላንሶችን ለሁሉም ክልሎች እና ለሁለት ከተማ አስተዳደር እንዲሁም ለስምንት ዩኒቨርስቲ ሆስፒታሎች አከፋፍያለሁ ብሏል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ በቅርቡ ሌሎች 407 አምቡላንሶች ወደ ሀገር ውስጥ ለመግባት በመጓጓዝ ላይ ናቸው ሲል አስታውቋል፡፡ ይህም ማለት ቀደም ሲል ከተሰራጩት 1200 አምቡላንሶች ጋር ሲደመር ከሁለት ሺህ በላይ ይሆናል ሲል ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ገልፆ የ1859 ተጨማሪ አምቡላንሶች በግዥ በሂደት […]

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ በአሜሪካ የነበረን ቆይታ አድካሚ ቢሆንም ስኬታማ ነበር ሲሉ ተናገሩ፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ በአሜሪካ የነበረን ቆይታ አድካሚ ቢሆንም ስኬታማ ነበር ሲሉ ተናገሩ፡፡ በአሁኑ ሰዓት ለመገኛኛ ብዙሀን እንደተናገሩት እንደ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ሁሉ የኤርትራ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን አንድ እንድትሆንም በኃላፊነት እንሰራለን ብለዋል፡፡ ለነበራቸው ቆይታ ድጋፍ ያደረጉትን ሁሉ አመስግነዋል፡፡

የአንጋፋው አርቲስት ፍቃዱ ተክለማርያም የቀብር ሥነ-ሥርዓት ዛሬ ሐምሌ 26 ቀን 2010 ዓ.ም ከቀኑ በ8 ሰአት አራት ኪሎ በሚገኘው ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ይፈጸማል።

የአንጋፋው አርቲስት ፍቃዱ ተክለማርያም የቀብር ሥነ-ሥርዓት ዛሬ ሐምሌ 26 ቀን 2010 ዓ.ም ከቀኑ በ8 ሰአት አራት ኪሎ በሚገኘው ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ይፈጸማል። ከጠዋቱ 4 ሰአት ጀምሮም ለበርካታ አመታት ባገለገለበት በብሄራዊ ቲያትር ቤተሰቦቹ፣ ወዳጅ ዘመዶቹ እና የሙያ አጋሮቹ በተገኙበት አሸኛኘት እንደሚደረግለት ተነግሯል፡፡

በወታደራዊ ስነ ምግባር ጥሰትና ኩብለላ ወንጀሎች ለተከሰሱ የመከላከያ ሰራዊት አባላት ምህረት ማድረጉን የመከላከያ ሚኒስቴር አስታወቀ።

በዚህም የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በቅርቡ ያጸደቀውን የምህረት አዋጅ መሰረት በማድረግ በወታደራዊ የስነ ምግባር ጥሰት ተከሰው በማረሚያ ቤት የሚገኙና ቀደም ሲል ከሃገር የኮበለሉ የሰራዊት አባላት ምህረት ተደርጎላቸዋል ብለዋል። የመከላከያ ኢንዶክትሪኔሽንና የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር ብርጋዴር ጀኔራል ኪዱ አለሙ፥ ለኢዜአ እንደገለጹት መንግስት በሃገር አቀፍ ደረጃ የጀመራቸውን የለውጥ እንቅስቃሴዎች ለማስቀጠል መከላከያ ሰራዊት ለውጡን በመደገፍ እየሰራ ነው። የምህረት አዋጁ […]