loading
አብዲ ሞሃመድ ዑመር (አብዲ ኢሌ) በቁጥጥር ስር ዋሉ፡፡

አብዲ ሞሃመድ ዑመር ትናንት ከክልሉ ፕሬዚዳንትነታቸው መነሳታቸው ቢገለጽም የኢትዮጵያ ሶማሌ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ መሪ ሆነው ይቀጥላሉ ተብሎ ነበር። የቀድሞው የክልሉ ፕሬዝዳንት በመከላከያ ሠራዊት አባላት በቁጥጥር ሥር እንዲውሉ ከተደረጉ በኋላ ጅግጅጋ ከሚገኘው ቤተ መንግሥት እንደተወሰዱ ምንጮች ለቢቢሲ ሶማልኛ ገልጸዋል። ከቅዳሜ አንስቶ በጂግጂጋ እና በክልሉ ሌሎች ከተሞች የተከሰተውን ሁከት ተከትሎ የሃገር መከላከያ ሠራዊት እና የፌደራል ፖሊስ ወደ […]

የኦሮሞ ህዝብ ዴሞክራሲያዊ ድርጅት /ኦህዴድ/ መጠሪያውን ወደ “ኦሮሞ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ” ለመቀየር ሀሳብ ማቅረቡ ተገለፀ።

የኦሮሞ ህዝብ ዴሞክራሲያዊ ድርጅት /ኦህዴድ/ መጠሪያውን ወደ “ኦሮሞ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ” ለመቀየር ሀሳብ ማቅረቡ ተገለፀ። የኦህዴድ የገጠር ፖለቲካና አደረጃጀት ዘርፍ ሀላፊ አቶ አዲሱ አረጋ እንደገለጹት፥ የኦህዴድን የስያሜ እና የአርማ ለውጥ ለማድረግ ሀሳብ ቀርቧል። በዚህም መሰረት አዲሱ የኦሮሞ ህዝብ ዴሞክራሲያዊ ድርጅት /ኦህዴድ/ መጠሪያ “የኦሮሞ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ” እንዲሆን ሀሳብ መቅረቡን ነው አቶ አዲሱ ያስታወቁት። ከዚህ በተጨማሪም ኦህዴድ ከዚህ […]

የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ ከእንግሊዝ ዓለም አቀፍ የልማት ድርጅት (ዲ ኤፍ አይ ዲ) ዋና ፀሃፊ ፔኒ ሞርዳውንት ጋር ተወያዩ።

የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ ከእንግሊዝ ዓለም አቀፍ የልማት ድርጅት (ዲ ኤፍ አይ ዲ) ዋና ፀሃፊ ፔኒ ሞርዳውንት ጋር ተወያዩ። የጠቅላይ ሚኒስትሩ ጽህፈት ቤት ሀላፊ አቶ ፍፁም አረጋ በቲዉተር ገጻቸዉ እንዳስታወቁት ውይይታቸውን በኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች እና ድህነት ቅነሳ ላይ ያተኮረ ነዉ ብለዋል፡፡የሁለቱ ሀገራት ጠንካራ ግንኙነትን ኢትዮጵያ እንደምታደንቅ በገጹ ተጠቅሷል፡፡

ከተለያዩ ሆስፒታሎች የተዉጣጡ የህክምና ባለሞያዎች በጅግጅጋ በተከሰተዉ ግጭት የተጎዱ ወገኖችን ለማከም ወደ ጅግጅጋ አቀኑ፡፡

ከተለያዩ ሆስፒታሎች የተዉጣጡ የህክምና ባለሞያዎች በጅግጅጋ በተከሰተዉ ግጭት የተጎዱ ወገኖችን ለማከም ወደ ጅግጅጋ አቀኑ፡፡ ሀኪሞቹ ከጥቁር አንበሳ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል፤ከየካቲት12 እና ከቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሊኔየም ሜዲካል ኮሌጅ የተወጣጡ መሆናቸዉን የጤና ጥበቃ ምኒስትሩ ዶክተር አሚር አማን በፌስቡክ ገጻቸዉ ገልጸዋል ወደ ጂግጂጋ የተጓዙት የጤና ባለሞያዎች ሃያ አራት ናቸዉ፡፡

የሰብአዊ መብት ጥሰት ደርሶብናል ያሉ 300 የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ካህናት ፤ዲያቆናትና አገልጋዮች ፍትህ ማግኘታቸዉን የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ገለጸ፡፡

ካህናቱ ከአስተዳደረዊ በደል በተጨማሪም ከስራ መባረር፤ የደሞዝ ክፍያን አለማግኘት፤ ያለቅድመ ዝግጅትና ፍትሃዊ ያልሆነ ዝውውር እንዲሁም ያለ ስራ መንገዋልል ከዋነኞቹ የመብት ጥሰቶች እንደሚካተቱ ቅሬታው የደረሰው የሰብአዊ መብት ኮሚሽን ተናግሯል፡፡ በኮሚሽኑ የከፍተኛ ኮሚሽነር ፅህፈት ቤት ሃላፊ አቶ ወንድሜነህ ዘውዱ እንዳሉት ኮሚሽኑ ላለፉት ሁለት ዓመታት ጉዳዩን ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ጋር በመሆን ሲመረምር ቆይቶ ተገቢውን ውሳኔ አስተላልፏል ብለዋል […]

በጂግጂጋ እና ሌሎች ከተሞች የሃገር መከላከያ ሰራዊት እያደረገ ያለው የማረጋጋት ስራ መቀጠሉን የኢፌዴሪ መከላከያ ሚኒስትር አቶ ሞቱማ መቃሳ ተናገሩ።

ሚኒስትሩ ጉዳዩን አስመልክተው በሰጡት መግለጫ፥ የሃገር መከላከያ ሰራዊት በጂግጂጋና በሌሎች የሶማሌ ክልል ከተሞች በመግባት የማረጋጋት ስራ እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል። አሁን ላይ ችግሩን በአንድ ጊዜ ለመመለስ ከባድ ቢሆንም መከላከያ ሰራዊት በከተሞች በመግባት ችግር ሲፈጠር መቆጣጠርና ማረጋጋት የሚያስችል ዝግጅት ማድረጉንም ነው የተናገሩት። በስፍራው የተፈጠረውን ችግር ሙሉ በሙሉ ለማረጋጋት የአካባቢው ነዋሪዎች በተለይም የሃገር ሽማግሌዎች ተሳትፎ ወሳኝ መሆኑንም ገልጸዋል። […]

በኢትዮጵያ የእንግሊዝ ኢምባሲ የመጀመርያ ዲግሪ ላላቸው ኢትዮጵያውያን ነፃ ትምህርት ዕድል ሊሰጥ ነው፡፡

በኢትዮጵያ የእንግሊዝ ኢምባሲ የመጀመርያ ዲግሪ ላላቸው ኢትዮጵያውያን ነፃ ትምህርት ዕድል ሊሰጥ ነው፡፡ በኢትዮጵያ የእንግሊዝ ኤምባሲ የመጀመርያ ዲግሪ ላላቸው ኢትዮጵያውን ነጻ የትምህርት ዕድል እንደሚሰጥ በኢትዮጵያ የእንግሊዝ ኢምባሲ ከፍተኛ የፖለቲካ ባለሙያ ጀሚ ኦርተን ገልጸዋል፡፡ ጀሚ ኦርተን ከአማራ ብዙኃን መገናኛ ጋር ባደረጉት ቆይታ የእድሉ ተጠቃሚ የሚሆኑት ተማሪዎች በማንኛውም የትምህርት ዘርፍ የመጀመርያ ዲግሪ ያላቸው አምልካቾች መሆኑን አስታውቀዋል፡፡ አመልካቾች ሁለት […]

በሀገር ደረጃ የሚሰራ የፎረንሲክ ማዕከል ባለመኖሩ አስቸኳይ ዉሳኔ የሚያስፈልጋቸዉን ጉዳዮች ቶሎ መርምሮ ለማወቅ እንቅፋት እየሆነ ነዉ ፡፡

በቅዱስ ጳዉሎስ ሆስፒታል የፎረንሲክ ሜዲስን ቴክኖሎጂ ሃላፊ ዶክተር እንየዉ ደባሽ ለአርትስ ቲቪ እንደተናገሩት የቅዱስ ጳዉሎስ ሆስፒታል የአስክሬን ምርመራ ፤የእድሜና የፆታ ጥቃት ሲደርስ በፎረንሲክ ክፍሉ ምርመራ ቢያደርግም፤ ከአባትነትና ከእናትነት ማረጋገጫ መሰል ዝርዝር የምረዛ ችግሮች ሲኖሩ ከሀገር ዉጪ ናሙና በመላክ ምርመራ ይደረጋል ብለዋል፡፡ በፎረንሲክ ምርመራ ባለሞያዎችን ወደ ህንድ በመላክ ለማሰልጠን ቢቻልም አገልግሎቱን በተገቢና በተቀላጠፈ መልኩ ለመስጠት መመርመሪያ […]

በጅግጅጋ ከተማ የተጎዱ ወገኖችን ለመርዳት የተላከው የጤና ባለሙያዎች ቡድን ትላንት ሀምሳ ዘጠኝ ለሚደርሱ ተጎጂዎች የህክምና እርዳታ አደረገ፡፡

ከታካሚዎች ዉስጥም ሰላሳ የሚሆኑት ቀዶ ጥገና የሚያስፈልጋቸው ናቸው ። ከነዚህ ዉስጥም ዘጠኝ ለሚሆኑ ተጎጂዎች ቀዶ ጥገና የተደረገ ሲሆን የተቀሩት በዛሬ እለት የቀዶ ጥገና ህክምና እርዳታ ይደረግላቸዋል ተብሏል። የጤና ጥበቃ ሚኒስትሩ ዶክተር አሚር አማን ለጤና ባለሙያዎቹ ምስጋና አቅርበዋል፡፡

በኤሌክትሪክ ኃይል ታሪፍ ላይ ጭማሪ ሊደረግ ነው::

በኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚዎች ላይ የታሪፍ ጭማሪ ለማድረግ አስፈላጊው ሂደት መጀመሩን የኢትዮጵያ ኢነርጂ ባለስልጣን አስታወቀ፡፡ ማሻሻያው ዝቅተኛ የኃይል ተጠቃሚዎችን አያካትትም ተብሏል፡ ቢቢሲ የኢትዮጵያ ኢነርጂ ባለስልጣን ዳይሬክተር የሆኑትን አቶ ጌታሁን ሞገስን አናግሮ እንደዘገበዉ የኤሌክትሪክ ታሪፍ ጭማሪው በተለያዩ ደረጃዎች አልፎ ተቀባይነት ሲያገኝ ተግባራዊ እንደሚሆን ተናግረዋል። አቶ ጌታሁን የታሪፍ ጭማሪ ማድረግ ያስፈለገበትን ምክንያት ለመጨረሻ ጊዜ የታሪፍ ጭማሪ ተደርጎ […]