loading
የኮሮና ቫይረስ  በ164 ሰዎች ላይ ሲገኝባቸው፤ የ5 ሰዎች ህይወት አልፏል

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 4፣ 2012  የኮሮና ቫይረስ  በ164 ሰዎች ላይ ሲገኝባቸው፤ የ5 ሰዎች ህይወት አልፏል፡፡ ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ በተደረገው 6 ሺህ 630 የላብራቶሪ ምርመራ 190 ሰዎች የኮሮና ቫይረስ እንደተገኘባቸው የጤና ሚኒስቴር አስታወቀ።በአጠቃላይ በኢትዮጵያ ቫይረሱ በምርመራ የተገኘባቸው ሰዎች ቁጥር 2 ሺህ 670 መድረሱንም የጤና ሚኒስትሯ ዶክተር ሊያ ታደሰ ዛሬ ባወጡት ሪፖርት አመላክተዋል። ቫይረሱ በምርመራ የተገኘባቸው […]

ጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ የኢትዮጵያ ሕዝብ ለአረንጓዴ ልማት እንዲነሳ ጥሪ አስተላለፉ::

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 4፣ 2012 ጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ የኢትዮጵያ ሕዝብ ለአረንጓዴ ልማት እንዲነሳ ጥሪ አስተላለፉ:: የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዓቢይ አህመድ አሻራችንን በማኖር ለኢትዮጵያ አረንጓዴ ምንጣፍ እንዘርጋ በማለት ጥሪ አቀረቡ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ በማህበራዊ ትስስር ገጾቻቸው ባስተላለፉት መልዕክት የአረንጓዴ ልማት ጥቅም በመረዳት መሥራት ያስፈልጋል። አረንጓዴ ዐሻራ ከሥነ ውበት በላይ ነው። የምንተነፍሰው አየር ነው። የምንጠቀመው እንጨት […]

በኢትዮጵያ የሰብዓዊ እርዳታ የሚያስፈልጋቸው ሰዎች ቁጥር ወደ 16 ሚሊየን ከፍ አለ::

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 4፣ 2012 በኢትዮጵያ የሰብዓዊ እርዳታ የሚያስፈልጋቸው ሰዎች ቁጥር ወደ 16 ሚሊየን ከፍ አለ::በኮሮና ቫይረስ ምክንያት በኢትዮጵያ የሰብዓዊ እርዳታ የሚያስፈልጋቸው ሰዎች ቁጥር ወደ 16 ነጥብ 5 ሚሊየን ከፍ ማለቱን በኢትዮጵያ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ፅህፈት ቤት አስታወቀ።  የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ከኢትዮጵያ መንግስት እና ከሌሎች አጋር አካላት ጋር በመተባበር የ2020 የሰብዓዊት እርዳታ ፍላጎቶች ላይ ክለሳ […]

የቀድሞው የሱዳን ፕሬዚዳንት ኦማር ሀሰን አልበሽር በወር 20 ሚሊዮን ዶላር ይከፈላቸው ነበር ተባለ::

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 4፣ 2012 የቀድሞው የሱዳን ፕሬዚዳንት ኦማር ሀሰን አልበሽር በወር 20 ሚሊዮን ዶላር ይከፈላቸው ነበር ተባለ:: የሀገሪቱ የፀረ ሙስና ኮሚቴ ሰነድ ሳገላብጥ አገኘሁት ብሎ ይፋ ባደረገው መረጃ አልበሽር ይህን ያክል መጠን ያለው ደሞዝ ይከፈላቸው የነበረው ካልታወቀ ምንጭ ነው፡፡ ሚድል ኢስት ሞኒተር እንደዘገበው አልበሽር ደቡብ ሰዳን ራሷን ችላ ሀገር እንስክትሆን ድረስ ወርሃዊ ደሞዛቸው 20 […]

ብራዚል በኮሮናቫይረስ ሳቢያ የሟች ዜጎቿ ቁጥር በዓለም ሁለተኛ ደረጃ እንድትቀመጥ አድርጓታል

አዲስ አበባ፣ሰኔ 7፣2012 ብራዚል በኮሮናቫይረስ ሳቢያ የሟች ዜጎቿ ቁጥር በዓለም ሁለተኛ ደረጃ እንድትቀመጥ አድርጓታል:: ደቡብ አሜሪካዊቷ ሃገር ብራዚል ዓርብ ዕለት በኮሮና ቫይረስ ህይወታቸው ያለፉ ዜጎች ቁጥርን ከፍ በከፍተኛ መጠን የመዘገበች መሆኑን ተከትሎ ሁለተኛ ደረጃን ከአውሮፓዊቷ እንግሊዝ ተረክባለች፡፡ ይሄንን ተከትሎ የዓለም ጤና ድርጅት የሀገሪቱ የጤና ስርዓት ትልቅ ጫና ውስጥ ይገኛል ብሏል፡፡የሀገሪቱ የጤና ሚኒስትር ዓርብ ዕለት የ24 […]

የሶማሊያው አልሻባብ የኮሮና ቫይረስ ማከሚያ ማዕከልን አቋቁመ::

አዲስ አበባ፣ሰኔ 7፣2012 የሶማሊያው አልሻባብ የኮሮና ቫይረስ ማከሚያ ማዕከልን አቋቁመ:: ሶማሊያ ላይ የመሸገው ፅንፈኛው የአልሸባብ ታጣቂ ቡድን፤ በሀገሪቱ ውስጥ የኮቪድ-19 ሕክምና ማዕከል ማቋቋሙን ገልፆ፤ የዓለም አቀፍ የጤና ባለሥልጣናትን ትንበያ በመጥቀስ በሽታው ከባድ ስጋት እንዳስከተለ ገልጧል ፡፡ ታጣቂ ቡድኑ መልዕክቶችን በሚያስተላልፈበት የአንዳሉስ ራዲዮ ስርጭት አል- ሸባብ የኮሮና ቫይረስ መከላከል እና እንክብካቤ ኮሚቴ በማቋቋም የኮቪድ-19 ማዕከል መገንባቱን […]

በአራተኛ ዙር 274 ዜጎች ከኩዌት ወደ አገራቸው መሸኘታቸዉን በኩዌት የሚገኘዉ የኢትዮጵያ ኤምባሲ አስታወቀ፡፡

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 8፣ 2012 በአራተኛ ዙር 274 ዜጎች ከኩዌት ወደ አገራቸው መሸኘታቸዉን በኩዌት የሚገኘዉ የኢትዮጵያ ኤምባሲ አስታወቀ፡፡ የኩዌት መንግሥት ያወጣውን የምህረት አዋጅ በመጠቀም ከኩዌት ወደ አገራቸው ለመመለስ ሲጠባበቁ የነበሩ 274 ዜጎች በአራተኛው ዙር ሰኔ 8 ቀን 2012 ዓ.ም ወደ አገራቸው ተሸኝተዋል።ዜጎቻችን በኩዌት ዓለም አቀፍ ኤርፖርት በአምባሳደር አብዱልፈታህ አብዱላሂ፣ ዲፕሎማቶችና ሰራተኞች እንዲሁም በኮሚኒቲ አመራሮች ሽኝት […]

በናይጀሪያ የቦኩሀራም ታጣቂዎች ባደረሱት ጥቃት 81 ሰዎች ተገደሉ::

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 8፣ 2012  በናይጀሪያ የቦኩሀራም ታጣቂዎች ባደረሱት ጥቃት 81 ሰዎች ተገደሉ:: ታጣቂዎቹ ሞንጉኖ እና ንጋንዛይ በተባሉት የሀገሪቱ አካባቢዎች ላውንቸር እና ሮኬቶችን ጭምር ታጥቀው ከባድ ጥቃት ማድረሳቸውን የአካባው ነዋሪዎች እና የእርዳታ ሰራተኞች ተናግረዋል፡፡ በጥቃቱ 20 የሚሆኑ የመንግስት ወታደሮች የተገደሉ ሲሆን በስፍራው የነበሩ ቀሪዎቹ ወታሮችም ተዋጊዎችን መመከት አቅቷቸው ሲሸሹ ታይተዋል ነው የተባለው፡፡ የመንግስት ወታደሮችን ጨምሮ […]

የቱርክ ተዋጊ ጄቶች በሰሜናዊ ኢራቅ በሚገኘው የፒኬኬ የጦር ሰፈር ድብደባ ፈጸሙ፡፡

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 8፣ 2012  የቱርክ ተዋጊ ጄቶች በሰሜናዊ ኢራቅ በሚገኘው የፒኬኬ የጦር ሰፈር ድብደባ ፈጸሙ፡፡የጦር ጄቶቹ ከቱርክ የተለያዩ የአየር ሃይል ማረፊያዎች በመነሳት የፒኬኬ ዋነኛ የጦር ካምፕን ጨምሮ በሰሜናዊ ኢራቅ የሚገኙ በርካታ ስፍራዎች ላይ ጥቃት አድርሰዋል፡፡እንደ ሀገሪቱ መከላከያ ሚኒስቴር ከሆነ የጦር ድብደባው በቱርክ የጦር ካምፕ ላይ የሚፈጸሙ ጥቃቶች እየጨመሩ በመምጣታቸው የተወሰደ የአፀፋ እርምጃ ነው፡፡የቱርክ መከላከያ […]

ከ90 ዓመታት በኃላ በህብረተሰቡ ተሳትፎ ሙሉ እድሳት የተደረገለት የነቀምቴ እስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የተሻለ አገልግሎት መስጠት ጀመረ ::

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 8 ፣ 2012 ከ90 ዓመታት በኃላ በህብረተሰቡ ተሳትፎ ሙሉ እድሳት የተደረገለት የነቀምቴ እስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የተሻለ አገልግሎት መስጠት ጀመረ ::የምስራቅ ወለጋ ዞን የመንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ለአርትስ በላከዉ መግለጫ የነቀምቴ እስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ለበርካታ ዓመታት እድሳት ሳይደረግለት የቆየና ለአመታት በብልሹ አሰራርና ለታካሚዎች አመቺ ባለመሆኑ ከህብረተሰቡ በርካታ ቅሬታዎችና ወቀሳዎችን ሲያስተናግድ እንደቆየ ገልጿል፡፡ሆስፒታሉ እድሳት የተደረገለት […]