loading
የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ተረኛ ችሎት በብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት የስራ ሃላፊ የነበሩት አቶ ተስፋዬ ኡርጌ ላይ ለተጨማሪ ምርመራ ከፖሊስ ከተጠየቀው 14 ቀን 8 ቀን ፈቀደ፡፡

የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ተረኛ ችሎት በብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት የስራ ሃላፊ የነበሩት አቶ ተስፋዬ ኡርጌ ላይ ለተጨማሪ ምርመራ ከፖሊስ ከተጠየቀው 14 ቀን 8 ቀን ፈቀደ፡፡

የአማራ ክልል ከፍተኛ አመራሮች ዛሬ መቀመጫዉን አስመራ ካደረገዉ ከአማራ ዲሞክራሲያዊ ኃይሎች ንቅናቄ (አዲኃን) ጋር ይወያያሉ፡፡

አዲኃን ባለፉት ስምንት ዓመታት መቀመጫውን ኤርትራ አድርጎ የኢትዮጵያን የፖለቲካ ስርዓት በመቃወም የትጥቅ ትግል ሲያደርግ የነበረ የፖለቲካ ፓርቲ ነዉ፡፡ የአማራ መገናኛ ብዙሃን እንዳስታወቀዉ አዲኃን ከመንግስት ጋር የሚያደርገዉ ድርድር ምን ጉዳዮች ላይ እንደሚያተኩር አስካሁን አልታወቀም፡፡ የአማራ ክልል ከፍተኛ አመራሮች ትላንት አስመራ መግባታቸዉ ይታወሳል፡፡

ባለፉት ዓመታት በተጠርጣሪዎችና በታራሚዎች አያያዝ ላይ ያሉ ችግሮች መሻሻል አልታየባቸውም ተባለ::

ይህን ያለው የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ከሚሽን በቢሸፍቱ ከተማ ለፌደራልና ክልል የጸጥታ ተቋማት ሀላፊዎች ባዘጋጀዉ ስልጠና ላይ ነዉ ። ስልጠናው በአትዮጵያ የሰብዓዊ መብቶችን ማክበርና ማስከበር ላይ ያተኮረ ሲሆን ለአምስት ቀናት የሚሰጥ ነው ። የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ዶክተር አዲሱ ገብረእግዚአብሄር ስልጠናዉን ሲከፍቱ ሰልጣኞቹ ሰብዓዊ መብት መከበርና ማስከበር ላይ ሃላፊነታቸውን በአግባቡ እንዲወጡ አሳስበዋል ። ስልጠናው […]

የተሽከርካሪ አደጋ አስከፊ እየሆነ በቁጥርም እያሻቀበ ነው፡፡

በአገራችን 2010 ዓ.ም 40ሺህ 998 የተሸከርካሪ አደጋ ደርሷል፡፡ 5ሺህ 118 ሰዎች በተሸከርካሪ አደጋ ሳቢያ ህይወታቸው አልፏል፡፡ 7ሺህ 754 ሰዎች ከባድ የአካል ጉዳት ደርሶባቸዋል፡፡ 7ሺህ 775 ሰዎች ቀላል የአካል ጉዳት ደርሶባቸዋል፡፡ ከ 920 ሚሊዮን 771 ሺህ ብር በላይ የተገመተ ንብረት ወድሟል፡፡ ባለፈው ዓመት 2009ዓ.ም የደረሰው አደጋ 38ሺህ 737 ነበር፡፡ አቶ ይግዛው ዳኘው የትራንስፖርት ባለስልጣን የህዝብ ግንኙነት […]

የትግራይ ክልል ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ስድስተኛ ሙት አመትን በማስመልከት ሀገራዊ የውይይት መድረክ ማዘጋጀቱን ገለፀ፡፡

የውይይት መድረኩ የፊታችን እሑድ ነሐሴ 13 ቀን ይካሔዳል፡፡ በትግራይ ክልል የፖሊሲ ጥናት ተቋም ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ፍሰሃ ሀብተ ፂዮን እንደተናገሩት የውይይት መድረኩ የመለስ ዜናዊ ስራዎች ላይ የሚያተኩር ሲሆን የሃገሪቱ የህዳሴ ጉዞ እንዲሁም ወቅታዊ ሁኔታዎች ይዳሰሱበታል፡፡ የክልሉ ኮሚዩኒኬሽን በድረ ገጹ እንዳስታወቀዉ ዶ/ር ፍሰሀ በመድረኩ ነባር እና አዲስ ከፍተኛ የመንግስት አመራሮች፣ምሁራን፣ፖለቲከኞች፣የተለያዩ ድርጅት ተወካዮች እነዲሁም የመቀሌ ከተማ እና […]

የኦሮሚያ የከተሞች ስራ ዕድል ፈጠራና ምግብ ዋስትና ኤጀንሲ በ2011 በጀት ዓመት ስራ አጥና በግል ስራ ላይ ለተሰማሩ ወጣቶች 3.283 ቢሊዮን ብር ለመስጠት አዘጋጅቻለሁ አለ፡፡

በዚህም 1.1 ሚሊዮን ወጣቶችን በ90 ማህበራት ለማደራጀት ተወስኗል፡፡ ከነዚህ መካከል 64 ሺህ የሚሆኑት ከመንግስት ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የሚመረቁ ናቸው፡፡ ለመፍጠር በተዘጋጀው የስራ ዕድል 52205 ሄክታር የከተማና የገጠር መሬት ተዘጋጅቷል፡፡ እንዲሁም 4648 አዳዲስ ሼዶች የሚገነቡ ይሆናል፡፡ የክልሉ ፕሬዝዳንት አቶ ለማ መገርሳ በወቅቱ እንዳሳወቁት ወጣቶች የተፈጠረላቸውን የስራ ዕድል ብቻ ሳይሆን በሃገር የኢኮኖሚ እድገት ላይ ተፅዕኖ ሊያሳድሩ እንደሚችሉ […]

የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ በሃገሪቱ አንዳንድ አካባቢዎች የሚስተዋለው የመንጋ ፍትህ እና አላስፈላጊ ሁከት ተቀባይነት የሌለው እና የህግ የበላይነትን አደጋ ውስጥ የሚጥል መሆኑን ገለጹ።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህን ያሉት በ11ኛው እነ 12ኛው ዙር የሰለጠኑ የመከላከያ መኮንኖችን ባስመረቁበት ወቅት ባደረጉት ንግግር ነው። በወቅቱ ባደረጉት ንግግር ድርጊቱ የህግ የበላይነትን የሚነድ በመሆኑ በአስቸካይ ሊቆም እንደሚገባው ገልጸዋል። ህብረተሰቡ በተለይም ወጣቱ የተሳሳተ መረጃን መሰረት በማድረግ ለህግ ቅድሚያ ሳይሰጥ የሚፈጽማቸው ድርጊቶች እየተገነባች ያለችን ሃገር ከማፍረስ ውጭ ዋጋ እንደሌለውም ጠቅሰዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ የህግ የበላይነት ለአንድ […]

ከስድስት ወራት በኋላ የሁሉም የስኳር ፕሮጀክቶች ግንባታ እንደሚጠናቀቅ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ ተናገሩ፡፡

ዶክተር አብይ ይህንን ያሉት በባህርዳር ከተማ ከብአዴን አመራሮች ጋር ባደረጉት ምክክር ላይ ነው፡፡ ባለፉት 9 ወራት የተሻለ ብሔራዊ መግባባትን ለመፍጠርና ኢኮኖሚያዊ ለውጦችን ለማምጣት ውጤታማ ተግባራት ተከናዉነዋል ብለዋል፡፡ በሀገሪቱ የተሻለ መግባባት ለመፍጠርም ከዲያስፖራው ማህበረሰብ ጋር የነበረውን ግንኙነት የማስተካከልና በሀይማኖቶች ውስጥ የነበረውን መከፋፈል የማጥፋት ስኬታማ ስራዎች ተሰርተዋል ብለዋል፡፡ በኢኮኖሚ ረገድም የውጭ ምንዛሬ በቤታቸው ያከማቹ ዜጐች ወደ ባንክ […]

በትምህርት ፖሊሲያችን ላይ ሁሉን አቀፍ ለዉጥ እንደሚያስፈልግ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ ተናገሩ፡፡

በትምህርት ፖሊሲያችን ላይ ሁሉን አቀፍ ለዉጥ እንደሚያስፈልግ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ ተናገሩ፡፡ የጠቅላይ ሚኒስትሩ ጽህፈት ቤት ሀላፊ አቶ ፍጹም አረጋ በቲዉተረ ገጻቸዉ እንዳስታወቁት ዶክተር አብይ ይህንን የተናገሩት ዛሬ የተጀመረዉን ሀገር አቀፍ የትምህርት ፖሊሲ ማሻሻያ ፍኖተካርታ ፎረምን በንግግር በከፈቱበት ወቅት ነዉ፡፡

የኢትዮጵያ የምግብ፣ የመድኃኒትና የጤና ክብካቤ አስተዳደርና ቁጥጥር ባለስልጣን ማሻሻያ ተደረገበት፡፡

በዚህም መሰረት ከዛሬ ጀምሮ ባለስልጣኑ ምግብና መድኃኒት ቁጥጥር ላይ ብቻ እንዲያተኩርና ቀደም ሲል በባለስልጣኑ ይሰጡ የነበሩ ሌሎች አገልግሎቶች ወደ ጤና ጥበቃ ሚኒስቴርና ሌሎች ተጠሪ ተቋማት እንዲዛወሩ መደረጉን የጤና ጥበቃ ሚኒስትሩ ዶክተር አሚር አማን በቲዉተርና በፌስቡክ ገጻቸዉ አስታዉቀዋል፡፡ በቀጣይም የስራ ኃላፊዎች፣ሰራተኞችና የአሰራር ስርዓቱ ላይ ትኩረት ሰጥተን እንሰራለን በማለት ጥራት ያለው የጤና አገልግሎት ለመስጠት በተያዘው አቅጣጫ መሰረት […]