loading
በሰኔ 16 የቦምብ ፍንዳታ ከተጠረጠሩት ግለሰቦች መካከል በአምስቱ ላይ ክስ ሊመሰረት ነው::

ለኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ ድጋፍ ለመስጠት ሰኔ 16 ቀን 2010 በአዲስ አበባ መስቀል አደባባይ በተዘጋጀ ሰልፍ ላይ ቦምብ በማፈንዳት ከተጠረጠሩ ግለሰቦች መካከል በአምስቱ ላይ ክስ ሊመሰረት ነው። መርማሪ ፖሊስ ምርመራውን አጠናቆ የምርመራ መዝገቡን ለአቃቤ ህግ ያሰረከበባቸው ተጠርጣሪዎች አብዲሳ ቀነኔ፣ ደሳለኝ ተስፋዬ፣ ጌቱ ግርማ፣ ህይወት ገዳ እና ባህሩ ቶላ ናቸው። የፌደራል ድንበር ተሻጋሪ ወንጀሎች […]

ኢትዮጵያ ለሽምግልና ልትቀመጥ ነዉ፡፡

ኢትዮጵያ የምትሸመግለዉ ኤርትራንና ጅቡቲን ነዉ፡፡ የዉጭጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አቶ መለስ አለም በሰጡት መግለጫ በሁለቱ ሀገራት መሀከል ያለዉ ችግር ተቀርፎ ሰላማዊ ግንኙነት እንዲሰፍን ኢትዮጵያ ለጅቡቲዉ ፕሬዝዳንት መልክት ልካለች ብለዋል፡፡ ሁለቱ ሀገራትም ለሽምግለና ለመቀመጥ መልካም ፍላጎትን አሳይተዋል ተብሏል፡፡

የ ኮድ 3 አጋዥ ታክሲ ባለቤቶች በሰልፍ አቤቱታ እያቀረቡ ነው ።

“ጥያቄአችን ካልተመለሰ ስራ እናቆማለን” ብለዋል ። በአዲስ አበባ ከተማ በአጋዥ ታክሲ ትራንስፖርት አግልግሎት ላይ የተሰማሩ ኮድ 3 ሚኒባስ ተሽከርካሪ ባለንብረቶች 22 አካባቢ በሚገኘው የአዲስ አበባ መንገድ ትራንስፖርት ፅህፈት ቤት ፊትለፊት አቤቱታ ለማቅረብ ስራ አቁመው ተሰልፈዋል። የተቃውሞው መነሻ “የተተመነው የታክሲ ታሪፍ ከተሰጠን ስምሪት ርቀት ጋር ባለመጣጣሙ ለኪሳራ እየዳረገን ስለሆነ ይሻሻልልን” የሚል ነው። በአሁኑ ሰአት በመቶዎች የሚቆጠሩ […]

ሱዳንና ኢትዮጵያ የድንበር ቁጥጥርን ለማስወገድ ተስማሙ::

ሱዳን ከኢትዮጵያ ጋር በሚያዋስናት ድንበር የምታደርገውን ቁጥጥር ለማቆም ቁርጠኛ መሆንዋን አስታውቃለች፡፡ ሱዳን ከውሳኔ ላይ የደረሰችው የሀገሪቱ ምክትል ፕሬዝዳንት ሀፊዝ አብዱል ራህማን ከኢፌዴሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ጋር በካርቱም በገቡት ስምምነት መሰረት ነው፡፡ የሀገራቱን ግንኙነት እንደሚያጠናክር የተነገረለት ስምምቱ እውን የሚሆነውም በሁለቱ ሀገራት የጋራ የቴክኒክ ኮሚቴ አማካኝነት እንደሆነ ተነግሯል፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የካቢኔ ሹም ሽር ሊያካሄድ ነው ተባለ፡፡

ሪፖርተር እንደዘገበዉ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ኢንጂነር ታከለ ኡማ የካቢኔ አባላት ሹም ሽር ሊያካሂዱመሆኑ እና ከመጠን በላይ በመስፋታቸው ምክንያት ለአሠራር አላመቹም የተባሉ መሥሪያ ቤቶች እንደሚታጠፉ ተነገሯል፡፡ ከፌዴራል መንግሥትና ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የተወጣጡ አመራሮች፣ እስከ ቀጣዩ ምርጫ ድረስ የካቢኔ አባል ሆነው የሚሠሩ ተሿሚዎች እየመለመሉ እንደሚገኙ ለማወቅ ተችሏል፡፡ በአሁኑ ወቅት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር […]

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ከሰሞኑ በኢትዮጵያ ሶማሌ ክልል የተፈጸመውን ድርጊት አወገዘች።

ቤተክርስትያንዋ ሰባት አብያተ ክርስትያናት ሙሉ በሙሉ ተቃጥለው የካህናት ህይዎት ማለፉንም ተናግራለች። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትሪያሪክ ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ዛሬ በሰጡት መግለጫ በሶማሌ ክልል በተፈጸመው ድርጊት ሳቢያ የሰው ህይዎት በመጥፋቱ ማዘናቸዉን ተናግረዋል። ከዚህ ባለፈም የሰላማዊ ሰዎች ህይዎት ማለፉንና በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች መፈናቀላቸውን ጠቅሰው፥ በሁኔታው የተሰማቸውን ሃዘን ገልጸዋል። አሁን ላይ አብረው በኖሩ ወንድማማች ህዝቦች […]

በድሬዳዋ ከተማ ከትናንት ጠዋት ጀምሮ በተከሰተው ግጭት የአሥር ሰዎች ህይወት ማለፉን፣ የአካል ጉዳት መድረሱን እና ንብረት መውደሙን ፖሊስስ ገለፀ፡፡

ግጭቱ በተከሰተበት ቀበሌ 09 እና አካባቢው በአሁኑ ሰዓት የተረጋጋ ሁኔታ መኖሩን የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ለአርትስ ቲቪ አስታውቋል፡፡ የሰዎች ህይወት ያለፈው ከእሳት ቃጠሎ ጋር በተገናኘ እንደሆነ የገለፀው ፖሊስ ከጉዳዩ ጋር ተያይዞ የተጠረጠሩ ሰዎችን በቁጥጥር ስር እያዋልኩ ነው ብሏል፡፡ የሰላም ተምሳሌቷ ድሬ ወደቀድሞ ሰላሟ እንድትመለስ ወጣቶችና የአገር ሽማግሌዎች አሁንም እየሰሩ እንደሆነ የገለፁልን ዋና ሳጅን ባንታለም ግርማ […]

የሶማሌ ክልል አዲሱ ፕሬዚዳንት አህመድ አብዲ መሀመድ የቀድሞው ፕሬዚዳንት አብዲ ሞሀመድ ኦማር ስልጣን እንዳስረከቡና ሽግግሩም በሰላም እንደተጠናቀቀ ለቢቢሲ ሶማልኛ ተናግረዋል።

የክልሉ አዲሱ ፕሬዚዳንት እንደተናገሩት የቀድሞው ፕሬዚዳንት ስልጣን ለመልቀቅ በመጠየቃቸው የስራ አስፈፃሚው ኮሚቴ ጥያቄያቸውን ተቀብሎ አዲሱን የክልሉ ፕሬዚዳንት እንደመረጠም ገልፀዋል። ሰሞኑን ከብዙ ሰዎች ሞት፣ አብያተ ክርስትያናት መቃጠልና ንብረት መውደም ጋር ተያይዞም በክልሉ የመከላከያ ሰራዊት የገባ ሲሆን በክልሉ ከነበረው አለመረጋጋትና ተቃውሞዎች ጋር ተያይዞም በማዕከላዊ መንግሥት ግፊት ምክንያት አብዲ ኢሌ ከስልጣን እንደወረዱ ብዙዎች አስተያታቸውን ቢሰጡም አዲሱ ፕሬዚዳንት ሲንከባለል […]