loading
በምስራቅ ጎጃም በደረሰ የመሬት መንሸራተት አደጋ የ8 ሰዎች ህይወት አለፈ፡፡

በምስራቅ ጎጃም ዞን ጎንቻ ሲሶ እነሴ ወረዳ በተከሰተ የመሬት መንሸራተት አደጋ የ8 ሰዎች ህይወት ማለፉን ፋና ዘግቧል። ጎንቻ ሲሶ እነሴ ወረዳ የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት እንዳስታወቀው፥ አደጋው የደረሰው ነሃሴ ነሀሴ 8 ቀን 2010 ዓ.ም ከሌሊቱ 7 ሰዓት አካባቢ ነው። በመሬት መንሸራተት አደጋውም የ8 ሰዎች ህይወት ሲያልፍ ስድስቱ የአንድ ቤተሰብ አባላት ሲሆኑ፥ ሁለቱ ደግሞ ስራ […]

የኦሮሚያ የከተሞች ስራ ዕድል ፈጠራና ምግብ ዋስትና ኤጀንሲ በ2011 በጀት ዓመት ስራ አጥና በግል ስራ ላይ ለተሰማሩ ወጣቶች 3.283 ቢሊዮን ብር ለመስጠት አዘጋጅቻለሁ አለ፡፡

በዚህም 1.1 ሚሊዮን ወጣቶችን በ90 ማህበራት ለማደራጀት ተወስኗል፡፡ ከነዚህ መካከል 64 ሺህ የሚሆኑት ከመንግስት ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የሚመረቁ ናቸው፡፡ ለመፍጠር በተዘጋጀው የስራ ዕድል 52205 ሄክታር የከተማና የገጠር መሬት ተዘጋጅቷል፡፡ እንዲሁም 4648 አዳዲስ ሼዶች የሚገነቡ ይሆናል፡፡ የክልሉ ፕሬዝዳንት አቶ ለማ መገርሳ በወቅቱ እንዳሳወቁት ወጣቶች የተፈጠረላቸውን የስራ ዕድል ብቻ ሳይሆን በሃገር የኢኮኖሚ እድገት ላይ ተፅዕኖ ሊያሳድሩ እንደሚችሉ […]

ለአዲስ ዓመት ከውጪ ሀገር ለሚመጡ ኢትዮጵያዉያን ዲያስፖራዎች 25 በመቶ የጤና አገልግሎት ቅናሽ ይደረግላቸዋል ተባለ፡፡

ጤና ጥበቃ ሚኒስቴር በሰው መግለጫ ከ ነሃሴ 14 ቀን 2010 ዓ.ም ጀምሮ የሚመጡ ኢትዮጲያዉያን ዲያስፖራዎች የአገልግሎት ቅናሹ ተጠቃሚ እንደሚሆኑ ተነግሯል፡፡ በጤና ጥበቃ ሚንስቴር የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ዶክተር ተገኔ ረጋሳ በፌደራል እንዲሁም በክልል የጤናውን ዘርፍ በተመለከተ ለሚመጡት ዲያስፖራዎች መረጃ እንዲሰጥ የተዋቀረ የድንገተኛ አስተባባሪ ቡድን መዘጋጀቱን ተናግረዋል፡፡ ዜጎች ወደ ሃገር ቤት ሲመጡ ከሚያገኙት የጤና አገልግሎት ባሻገር […]

የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ በሃገሪቱ አንዳንድ አካባቢዎች የሚስተዋለው የመንጋ ፍትህ እና አላስፈላጊ ሁከት ተቀባይነት የሌለው እና የህግ የበላይነትን አደጋ ውስጥ የሚጥል መሆኑን ገለጹ።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህን ያሉት በ11ኛው እነ 12ኛው ዙር የሰለጠኑ የመከላከያ መኮንኖችን ባስመረቁበት ወቅት ባደረጉት ንግግር ነው። በወቅቱ ባደረጉት ንግግር ድርጊቱ የህግ የበላይነትን የሚነድ በመሆኑ በአስቸካይ ሊቆም እንደሚገባው ገልጸዋል። ህብረተሰቡ በተለይም ወጣቱ የተሳሳተ መረጃን መሰረት በማድረግ ለህግ ቅድሚያ ሳይሰጥ የሚፈጽማቸው ድርጊቶች እየተገነባች ያለችን ሃገር ከማፍረስ ውጭ ዋጋ እንደሌለውም ጠቅሰዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ የህግ የበላይነት ለአንድ […]

ባለፉት 24 ዓመታት በኢትዮጵያ በትምህርትና ስልጠና ሥርዓት በታዩ ችግሮች ዙርያ ዛሬ ውይይት ይደረጋል

የኢፌዲሪ የትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶክተር ጥላዬ ጌቴ በጽህፈት ቤታቸው በሰጡት መግለጫ ከዛሬ ጀምሮ የሚደረገው የውይይት መድረክ ዋነኛ ዓላማ ለፍኖተ-ካርታው ዝግጅት እንዲረዳ በተዘጋጀው የመጀመሪያ ደረጃ ረቂቅ ጥናት ዙሪያ ውይይት በማድረግ ለፍኖተ-ካርታው ዝግጅት የሚረዳ ተጨማሪ ግብዓት ለማሰባሰብ መሆኑንም ገልፀዋል፡፡ የማሻሻያ ሀሳቦች ዙሪያ በሚደረገው ውይይት በተሳታፊዎች የሚቀርቡ ተጨማሪ የማሻሻያ ሀሳቦች በቂ ውይይት ከተደረገባቸውና መግባባት ከተደረሰባቸው በኋላ ለ15 ዓመታት […]

የዘንድሮ አረፋ በዓል በአዲስ አበባ በአንድነት በአንድ ቦታ በስቴዲም ይከበራል፡፡

በነገው ዕለት የሚከበረው ዒድ አል አድሃ አረፋ ከሌሎች ግዜያቶች በተለየ መልኩ በአንድነት እና በፍቅር ስሜት እንድሚከበር ነዉ የአድስ አበባ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክርቤት ፕሬዝደንት ሼህ መሀመድ ሸሪፍ ሃሰን ለአርትስ ቲቪ የተናገሩት፡፡ የዘንድሮው አረፋ ልዩነታችን ተገፎ በአንድነት እና በእርቅ ማከበራችን ለየት ያደርገዋል ብለዋል፡፡ በዓሉም ‹ሰላም እና አንድነት ለኢትዮጵያ›› በሚል መሪ-ቃል እንደሚከበርም ሼህ መሀመድ ነግረዉናል፡፡ የ አረፋ […]

በትምህርት ፖሊሲያችን ላይ ሁሉን አቀፍ ለዉጥ እንደሚያስፈልግ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ ተናገሩ፡፡

በትምህርት ፖሊሲያችን ላይ ሁሉን አቀፍ ለዉጥ እንደሚያስፈልግ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ ተናገሩ፡፡ የጠቅላይ ሚኒስትሩ ጽህፈት ቤት ሀላፊ አቶ ፍጹም አረጋ በቲዉተረ ገጻቸዉ እንዳስታወቁት ዶክተር አብይ ይህንን የተናገሩት ዛሬ የተጀመረዉን ሀገር አቀፍ የትምህርት ፖሊሲ ማሻሻያ ፍኖተካርታ ፎረምን በንግግር በከፈቱበት ወቅት ነዉ፡፡

የኢትዮጵያ የምግብ፣ የመድኃኒትና የጤና ክብካቤ አስተዳደርና ቁጥጥር ባለስልጣን ማሻሻያ ተደረገበት፡፡

በዚህም መሰረት ከዛሬ ጀምሮ ባለስልጣኑ ምግብና መድኃኒት ቁጥጥር ላይ ብቻ እንዲያተኩርና ቀደም ሲል በባለስልጣኑ ይሰጡ የነበሩ ሌሎች አገልግሎቶች ወደ ጤና ጥበቃ ሚኒስቴርና ሌሎች ተጠሪ ተቋማት እንዲዛወሩ መደረጉን የጤና ጥበቃ ሚኒስትሩ ዶክተር አሚር አማን በቲዉተርና በፌስቡክ ገጻቸዉ አስታዉቀዋል፡፡ በቀጣይም የስራ ኃላፊዎች፣ሰራተኞችና የአሰራር ስርዓቱ ላይ ትኩረት ሰጥተን እንሰራለን በማለት ጥራት ያለው የጤና አገልግሎት ለመስጠት በተያዘው አቅጣጫ መሰረት […]

አርሷደሯ ጌሪ አሜሪካ ተብሎ ለሚጠራው የእህል ፈጅ ትል መድሀኒት አገኙ፡፡

አርሷደሯ ወ/ሮ ታቦቴ አባተ በቦኖ በደሌ ዞን አርሶ አደር ናቸው። ከችግራቸው በመነሳትም ጌሪ አሜሪካ ለተባለ ትል አዲስ የትል ማጥፊያ ፈጥረዋል። የሳይንስና ቴክኖሎጂ ኢንፎርሜሽን ሴንተር በድረ ገጹ እንዳስታወቀዉ ጌሪ አሜሪካ በቆሎን በብዛት የሚያጠቃ ትል ነው።ትሉ ቁጥጥር ካልተደረገበት በበቆሎ ምርት ላይ ከባድ ጉዳት ያደርሳል። በአንድ ሌሊት በ1500 እጥፍ ሊራባ ይችላል። ወ/ሮ ታቦቴ ታዲያ ይህን ትል የሚገድል መድሀኒት […]

የሀጂ ተጓዦች ከከባድ ዝናብ ጋር እየታገሉ ነው፡፡

ማንኛውም ሙስሊም በህይዎት ዘመኑ አንድ ጊዜ ሊያሳካው የሚመኘውን የሀጂ ስነ ስርዓት ለመታደም ከ2 ሚሊዮን በላይ አማኞች ሳውዲ አረቢያ ገብተዋል፡፡ ሮይተርስ እንደዘገበው እምብዛም ዝናብ በማታውቀው ሳውዲ አረቢያ እየዘነበ ያለው ነጎድጓዳማ ዝናብ የጎርፍ አደጋና ውሀ ወለድ በሽታ እንዳያደስከትል ተሰግቷል፡፡ የሀገሪቱ የጤና ሚንስቴር ግን እስካሁን ምንም ዓይነት ችግር አላጋጠመም የታየ የህመም ምልክትም የለም የሚል መግለጫ ሰጥቷል፡፡