loading
ሱዳን ከኢትዮጵያ ጋር ጊዜያዊ ስምምነት ለማድረግ ጠየቀች፡፡

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 8፣ 2013 ሱዳን ከኢትዮጵያነ ጋር በግድቡ ዙሪያ ጊዜያዊ ስምምት ለማድረግ ዝግጁ ነኝ አለች፡፡ የሱዳኑ የውሃ ሚኒስትር ያሲር አባስ ካርቱማ ላይ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ ኢትዮጵያ ሁለተኛውን ዙር የውሃ ሙሌት ከመጀመሯ አስቀድሞ በቅድመ ሁኔታ ላይ የተመሰረተ ጊዜያዊ ውል ማሰር አለብን ብለዋል፡፡ ሚንስትሩ እንደ ቅድመ ሁኔታ አድርገው ካነሷው ነጥቦች መካከልም ከአሁን ቀደም የደረስንባቸው ስምምነቶችና […]

ላውረን ባግቦ ወደ ሀገራቸው ሲገቡ ፕሬዚዳንታዊ አቀባበል ሊደረግላቸው መሆኑ ተሰማ፡፡

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 8፣ 2013  የቀድሞው የኮትዲቯር ፕሬዚዳንት ላውረን ባግቦ ከአስር ዓመት ስደት በኋላ በመጭው ሀሙስ ወደ ሀገራቸው እንደሚገቡ የፓርቲያቸው ዋና ፀሃፊ ተናግረዋል፡፡ በሀገር ውስጥ የሚንቀሳቀሰው ፓርቲያቸው ፖፑላር ፍሮንት በሰጠው መግለጫ ባግቦ አውሮፕላን ማረፊያ እንደደረሱ በቪአይፒ ክፍል እንዲያርፉ ተደርጎ ፕሬዚዳንታዊ የክብር አቀባበል ይደረግላቸዋል ብሏል፡፡ የቀድሞ ተቀናቃኛቸውና የወቅቱ ፕሬዚዳንት አላሳኒ ኦታራ ባግቦ ወደ ሀገራቸው መመለሳቸው […]

ናይጄሪያ ለ12 ዓመታት በዘለቀው ግጭት ከ300 ሺህ በላይ ህፃናት መገደላቸውን የተባበሩት በ መንግስታት ድርጅት ይፋ አደረገ፡፡

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 18፣ 2013 በሰሜናው ምስራቅ የሀገሪቱ ክፍል ለዓመታት በዘለቀው ግጭት በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ ቁጥራቸው ወደ 350 ሺህ ለሚጠጋ ህፃናት ሞት ምክንያት ሆኗል ብሏል ድርጅቱ፡፡ አልጀዚራ እንደዘገበው ከሟቾቹ መካከል የሚበዙት ዕድሜያቸው ከአምስት ዓመት በታች መሆኑን በሪፖርቱ ተመላክቷል፡፡ ቦኩ ሃራም የተባለው ታጣቂ ቡድን እንደ አውሮፓዊያኑ አቆጣጠር በ2009 የተደራጀ ጥቃት ማድረስ ከጀመረ ወዲህ ከ2 ሚሊዮን […]

የመሪያቸው ሸንቃጣነት ያሳሰባቸው ሰሜን ኮሪያዊያን…

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 22፣ 2013 ሰሜን ኮሪያዊያን የመሪያቸውን ክብደት መቀነስ ከጤናቸው ሁኔታ ጋር አያይዘው ሀሳብ ገብቷቸዋል ተባለ፡፡ ለወትሮው በሰፋፊ ልብሶቻቸው ፈርጠም ባለ ሰውነታቸው የሚታወቁት ፕሬዚዳንት ኪም ጆንግ ኡን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ሸንቀጥ ብለው ታይተዋል ነው የተባለው፡፡ ይህ ደግሞ ለሰሜን ኮሪያዊያን እንደ መልካም ዜና እንደማይቆጠር መገናኛ ብዙሃን በስፋት እየዘገቡት ይገኛሉ፡፡ የሀገሪቱ ቴሌቭዥን ጣቢያ በሳምንቱ መጨረሻ […]

የቻይና መንግስት ህገ ወጥ አዘዋዋሪ ነው- አንቶኒ ብሊንከን

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 25፣ 2013 አሜሪካ ቻይናና ሩሲያን ጨምሮ ከ10 በላይ ሀገሮችን በህገ ወጥ ሰዎች ዝውውርና በግዳጅ የጉልበት ብዝበዛ ከሰሰች፡፡ የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን በሰጡት መግለጫ ከሩሲያና ቻይና በተጨማሪ ማይናማር እና ቱርክ በዚሁ ተግባር ይሳተፋሉ የሚል ወቀሳ አቅርበዋል፡፡ ብሊንከን በተለይ ሺንጂያንግ ግዛት አካሂዶታል ያሉትን የጅምላ እስር እና ተያያዥ ተግባራትን በመጥቀሽ የቻይና መንግስት […]

የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት 6ኛ ዓመት የስራ ዘመን 4ኛ ልዩ ስብሰባውን እያካሄደ ነው::

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 28፣ 2013 ምክር ቤቱ ልዩ ስብሰባውን የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በተገኙበት ነው እያካሄደ የሚገኘው፡፡ ምክር ቤቱ በልዩ ስብሰባው የፌዴራል መንግስትን የ2014 በጀት ዓመት ረቂቅ በጀት ላይ ተወያይቶ እንደሚያፀድቅ ይጠበቃል፡፡ በምክር ቤቱ ስብሰባ መክፈቻ ላይ የሃገር መከላከያ ሰራዊት ላበረከተው አስተዋፅኦ የምክር ቤቱ አባላት አድናቆታቸውን በጭብጨባ ገልፀዋል፡፡ በጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት መሰብሰቢያ […]

በአዲስ አበባ ትላንት በተከሰተ የጎርፍ አደጋ ከአንድ ቤተሰብ 5 ሰዎች ህይወታቸዉ አልፏል-ተጎጂዎች

አዲስ አበባ፣ ነሃሴ 12፣2013  በመዲናዋ ትናንት በተከሰተ የጎርፍ አደጋ እስካሁን የ7 ሰዎች ህይወት አለፈ:: የአዲስ አበበ እሳትና ድንገተኛ አደጋዎች ስራ አመራር ኮሚሽን ኮሚሽነር ሰለሞን ፍሰሃ ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት እንደገለጹት÷ በተከሰተው አደጋ በህይወት እና ንብረት ላይ የደረሱ ጉዳቶች እየተጣሩ ነው፡፡ እስካሁን በአደጋው የ7 ሰዎች ህይወት ማለፉን የገለጹት ኮሚሽነሩ÷አጠቃላይ የደረሰው ጉዳት ዛሬ ከሰዓት ይፋ እንደሚደርግም ጠቁመዋል፡፡ በመካነየሱስ […]

የአሸባሪው ጌታቸው ረዳ ወንድም ሃይለ ረዳ መልዕክት፡፡

አዲስ አበባ፣ ነሃሴ 14፣2013 አሸባሪው ህወሓት ኢትዮጵያን አፈርሳለሁ እንቅስቃሴ የአገር ክህደት መሆኑን የጌታቸው ረዳ ወንድም ሃይለ ረዳ ገለጹ:: በአፋር ክልል ሰመራ ዩኒቨርሲቲ የስነ ዜጋ መምህሩ ሃይለ ረዳ፤ አሸባሪው ህወሓት የትግራይ ን ህዝብ ከአጎራባች ክልሎች ጋር ደም ለማቃባት ትንኮሳ ማድረጉ ፍፁም ተቀባይነት የለውም ሲሉም ገልጸዋል። የሽብር ቡድኑ የአገር ዳር ድንበር የሚጠብቀውን የአገር መከላከያ ሰራዊት ሰሜን ዕዝን […]

በአሜሪካ ሕፃናት በዴልታ ኮቪድ 19 ቫይረስ እየተጠቁ መሆኑ በአሜሪካ ሕፃናት በኮቪድ 19 ቫይረስ እየተጠቁ መሆኑ ተጠቆመ፡፡

አዲስ አበባ፣ ነሃሴ 18፣2013 በአሜሪካ ሕፃናት በዴልታ ኮቪድ 19 ቫይረስ እየተጠቁ መሆኑ በአሜሪካ ሕፃናት በኮቪድ 19 ቫይረስ እየተጠቁ መሆኑ ተጠቆመ፡፡ የአሜሪካ ፔዲያትሪክስ አካዳሚ እና የሕፃናት ሆስፒታል ማሕበር ባወጡት ሪፖርት÷ ባሳለፍነው ሳምንት ብቻ በሀገሪቱ ወደ 94 ሺህ የሚጠጉ ሕፃናት በቫይረሱ ተጠቅተዋል ፡፡ ሉዚያና እና ፍሎሪዳ በርካታ በኮቪድ 19 ቫይረስ የተጠቁ ሕፃናት ሪፖርት የተደረገባቸው አካባቢዎች እንደሆኑም ተመላክቷል፡፡ […]

የደቡብ ዕዝ ወታደራዊ ፍርድ ቤት የዕዙ የሰራዊት አባላት ሆነው ለአሸባሪው ህወሓት ሲሰሩ በነበሩ የሰራዊት አባላት ላይ የጥፋተኝነት ውሳኔ ሰጥቷል፡፡

አዲስ አበባ፣ ነሃሴ 19፣2013 የደቡብ ዕዝ ወታደራዊ ፍርድ ቤት የዕዙ የሰራዊት አባላት ሆነው ለአሸባሪው ህወሓት ሲሰሩ በነበሩ የሰራዊት አባላት ላይ የጥፋተኝነት ውሳኔ ሰጥቷል፡፡ የሰራዊት አባላቱ ለህገ-መንግስቱና ለሀገራቸው የገቡትን ቃል ኪዳን ወደጎን በመተው የሰራዊቱን አጠቃላይ እንቅስቃሴዎች አደጋ ላይ የሚጥሉና የትግራይ ልዩ ሃይልን የሚያጠናክሩ ተግባራትን ሲያከናውኑ መቆየታቸው በችሎቱ ተነስቷል፡፡ በተለይም የሰራዊቱን ልዩ ልዩ ምስጢራዊ ሰነዶች ለትግራይ ልዩ […]