loading
ሞቃዲሾ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ባለ ስልጣን ከሀገሯ እንዲወጡ ትእዛዝ ሰጠች

የሶማሊያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ባወጣው መግለጫ በድርጅቱ የሶማሊያ ልዩ ልኡክ ኒኮላስ ሀይሶም ሀገሪቱን ለቀው እንዲወጡ የምናደርገው በውስጥ ጉዳያችን ጣልቃ በመግባታቸው ነው ብሏል፡፡ ልዩ ተወካዩ የቀድሞው የአልሸባብ ቃል አቀባይ ሸይክ ሙክታር ሮቦውን  መታሰር ጨምሮ ሌሎች የጥትታ ጉዳዮችን አስመልክተው ተደጋጋሚ ደብዳቤዎችን በመፃፍ የስልጣን ገደባቸውን አልፈዋል ብሏል መግለጫው፡፡ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ሶማሊያ ከእርስበርስ ጦርነት ወጥታ የተረጋጋች ሀገር እድትሆን […]

ፕሬዝዳንት ሺ በታይዋን የመጣብንን አንታገሰውም አሉ

የቻይናው ፕሬዝዳንት ሽ ጂንፒንግ ታይዋን የቻይና አካል መሆኗን ታሪክም ህግም ይደግፈናል፣ ከአንድ ቻይና ፖሊሲያችን አንድ ጋት አናፈግፍግም ብለዋል፡፡ ሺ ይህን ያሉት ቻይና ከታይዋን ጋር የምታደርገውን ጦርነት አቁማ በሰላም የመዋሀድ ሀሳብ ያቀረበችበትን 40ኛ ዓመት በምታከብርበት ወቅት ነው፡፡ አንዲት ጠንካራ ቻይና ሳይሆን ሁለት ቻይናዎች እንዲኖሩ የሚያሴሩትን ሁሉ አጥብቀን እንቃወማለን ያሉት ፕሬዝዳንቱ ታይዋንን የቻይና አካል ለማድረግ ሁሉንም የእርምጃ […]

የታላቁን የህዳሴ ግድብ ግንባታ ለማፋጠን የሚያስችል ስምምነት ተፈረመ

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ኮርፖሬሽን ጂኢ ሃይድሮ ፍራንስ ከተባለ ኩባንያ ጋር የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን ግንባታ ለማፋጠን የሚያስችል ስምምነት መፈራረሙ ተገለጸ፡፡ ጃኢ ሃይድሮ ፍራንስ በቅድሚያ ሃይል እንዲያመነጩ ታስበው ዲዛይን የተደረጉትን ሁለት ተርባይኖችን ጨምሮ አምስት የኃይል ማመንጫ ዩኒቶች ለማምረት፣ ለመግጠምና ለመፈተሸ ኮሚሌክስ ከተባለ ድርጅት ጋር በጥምረት የ53 ነጥብ 9 ሚሊዮን ዩሮ ስምምነት ፈርሟል። ጂኢ ሃይድሮ ቀደም ሲል […]

321 የቡራዩ ተጠርጣሪዎች ከእስር ሲቀለቀቁ 109 ደግሞ ክስ ተመሰረተባቸው።530 ታራሚዎች ይቅርታ ተደርጎላቸዋል

የፌዴራል ዐቃቢ ህግ በሰጠው መግለጫ በያዝነው ዓመት መጀመሪያ ላይ በቡራዩ ከተማ በተቀሰቀሰው ጥቃት ተሳትፈዋል ባላቸው 109 ተጠርጣሪዎች ላይ ክስ መመስረቱን ተናግሯል። ከነዚህም መካከል 81 ተጠርጣሪዎች በተገኙበት 28ቱ ደግሞ በሌሉበት ክስ የተመሰረተባቸው መሆኑን ነው የአቃቤ ህግ መግለጫ የሚያስረዳው፡፡ በቁጥጥር ስር ያልዋሉትን 28 ተጠርጣሪዎች ፖሊስ ለማደን የፍርድ ቤት ማዘዣ እንደወጣባቸው በመግለጫው ተካቷል፡፡ የፌዴራል አቃቤ ህግ የህዝብ ግንኙነት […]

የቻይናው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዎንግ ዩ ከጠቅላይ ሚኒስትር አብይ እና ከፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ጋር ተወያዩ

በኢትዮጵያ ይፋዊ የስራ ጉብኝት በማድረግ ላይ የሚገኙትን የቻይና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዋንግ ዪ ከኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ እና ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ ጋር ተገናኝተው ተወያይተዋል። ውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ከሁለቱ የሃገሪቱ ታላላቅ ባለስልጣናት ጋር በነበራቸው ውይይት በሁለቱ ሀገራት መካከል ባለው የጠበቀ የረጅም ጊዜ ግንኙነት እና ቻይና ለኢትዮጵያ በምታደርገው ድጋፍ ዙሪያ ተነጋግረዋል። ዋንግ ዩ ከጠቅላይ ሚኒስትር […]

አስተዳደሩ ከ134 ሺህ በላይ የጋራ መኖሪያ ቤቶችን ለተጠቃሚዎች ለማስተላለፍ አቅዷል

አስተዳደሩ ከ134 ሺህ በላይ የጋራ መኖሪያ ቤቶችን ለተጠቃሚዎች ለማስተላለፍ አቅዷል የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ከንቲባ ኢንጂነር ታከለ ኡማ እንዳሉት ቤቶቹ የሚተላለፉት በሚቀጥሉት 8 ወራት ውስጥ ነው። ምክትል ከንቲባው ይህንን የገለጹት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት 6ኛ የስራ ዘመን 1ኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ የ2011 በጀት ዓመት የ6 ወር እቅድ አፈፃፀም ሪፖርት ባቀረቡበት ወቅት ነው። ምክትል […]

በአብዲ መሃመድ ዑመር ላይ የተጀመረው ምርመራ በ14 ቀናት ተራዘመ

በአብዲ መሃመድ ዑመር ላይ የተጀመረው ምርመራ በ14 ቀናት ተራዘመ ፖሊስ በፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ በቀረቡት የሶማሌ ክልል የቀድሞው ፕሬዚዳንት አብዲ ሙሃመድ ኡመር ላይ የጠየቀውን ተጨማሪ 14 ቀናት የምርመራ ጊዜ ችሎቱ ፈቀደ። ችሎቱ የሶማሌ ክልል የቀድሞው ፕሬዚዳንት የነበሩት አብዲ ሙሃመድ ዑመርና ከሳቸው ጋር በመተባበር በተጠረጠሩት ሶስት ተከሳሾች ላይ ባለፉት14 ቀናት የተካሄደውን የምርመራ ውጤት አድምጧል፡፡ […]