loading
በህንድ በ24 ሰዓታት ውስጥ ክብረ ወሰን የሆነ የኮሮናቫይረስ ሞት ተመዘገበ::

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 11፣ 2013 በህንድ በ24 ሰዓታት ውስጥ ክብረ ወሰን የሆነ የኮሮናቫይረስ ሞት ተመዘገበ በህንድ እየተባባሰ የመጣውን የኮሮናባይረስ ወረርሽኝ መቆጣጠር ያቃታቸው ጠቅላይ ሚንስትር ናሬንድራ ሞዲ በህዝባቸው ዘንድ የነበራቸውን አመኔታ ዝቅ እንዲል አድርጎባቸዋል፡፡ በ24 ሰዓታት ውስጥ 4 ሽህ 529 ዜጎቿን በቫይረሱ የተነጠቀቸው ህንድ አሁንም በወረርሽኙ ጠንካራ ክንድ እየተደቆሰች ትገኛለች፡፡በየቀኑ በአማካይ ከ250 ሺህ በላይ ሰዎች […]

የቴክኖው CAMON 17 ሰልፊ ላይ ባውጠነጠነ አስገራሚ ዘጋቢ ፊልም በመታገዝ ወደገበያ ገብቱዋል::

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 12፣ 2013 የቴክኖው CAMON 17 ሰልፊ ላይ ባውጠነጠነ አስገራሚ ዘጋቢ ፊልም በመታገዝ ወደገበያ ገብቱዋል::ይህ ፈጠራ የታከለበት በፊልም የታገዘው የቴክኖ የማስመረቂያ ፕሮግራም ድርጅቱ ምርቱን ከማስተዋወቅ ባለፈ በኢንዱስትሪ፣ በማኅበራዊና በሰብዓዊነት ላይ የበለጠ ጥረት ለማድረግ ያለውን ፍላጎት የሚያንጸባርቅ ነው:: ይህ ደግሞ ድርጅቱ በአለማችን ላይ በዘርፉ ቁንጮ እየሆነ መምጣቱን ይጠቁማል:: በአዲሱ ትውልድ በአለም አቀፍ ደረጃ […]

ከአንድ ሚሊዮን አምስት መቶ ሺ በላይ ሰዎች የኮቪድ 19 ክትባት ተከትበዋል ተባለ::

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 12፣ 2013 ከአንድ ሚሊዮን አምስት መቶ ሺ በላይ ሰዎች የኮቪድ 19 ክትባት ተከትበዋል ተባለ:: የጤና ሚኒስቴር በየ24 ሰዓቱ በሚያወጣው የኮቪድ 19 ወቅታዊ መረጃ መሰረት በኢትዮጵያ ከአንድ ሚሊዮን አምስት መቶ ሺ በላይ ሰዎች የኮቪድ 19 ክትባት መከተባቸውን ገልጿል፡፡ በተጨማሪም 2 መቶ22 ሺ 5 መቶ 60 ሰዎች ከበሽታው ማገገማቸውን ሪፖርቱ አትቷል፡፡ ሚኒስቴር መስሪያቤቱ […]

የኢትዮ ቴሌኮምን ድርሻ በከፊል ወደ ግል ለማዞር የተደረገ ምክክር::

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 12፣ 2013  ጠ/ሚ ዐቢይ የኢትዮ ቴሌኮምን ድርሻ በከፊል ወደ ግል ለማዞር ከተቋቋመው አማካሪ ምክር ቤት አባላት ጋር ተወያዩ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ለሁለት የቴሌኮም ኦፕሬተሮች ፈቃድ ለመስጠት እየተሰራ ባለው ስራ ዙሪያ ከአማካሪ ምክር ቤት አባላት ጋር መከሩ።ውይይቱ አዲስ የቴሌኮም ፈቃድ በመስጠት ሂደቱ ዙሪያ የኢትዮ ቴሌኮምን ድርሻ በከፊል ወደ ግል ለማዞር ከተቋቋመው […]

19 ክትባት ለሚከተቡ ሰዎች የአንድ ሚሊዮን ዶላር ሎተሪ::

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 12፣ 2013 የኮቪድ ኦሃዮ በተሰኘችው አሜሪካዋ ክፍለ ሃገር የኮቪድ 19 ክትባት ለሚከተቡ ሰዎች አንድ ሚሊዮን ዶላር የሚያስገኝ የሎተሪ ቁጥር እንደሚሰጣቸው ከተገለፀ በኋላ የተከታቢዎች ቁጥር በእጅጉ መጨመሩ ተገለፀ:: የኦሃዮ ክፍለ ሃገር አስተዳዳሪ ማይክ ዲዋይን በክትባቱ ላይ ጥርጣሬ ያላቸውን ሰዎች ለማበረታታትና የሚከተቡ ሰዎችን ቁጥር ለመጨመር ለእያንዳንዱ ክትባቱን የተከተበ ሰው አንድ ሚሊዮን ዶላር የሚያስገኝ […]

የህዳሴው ግድብ የሰላም ፕሮጀክት ነው” ደቡብ-ሱዳን

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 14፣ 2013  ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ለሶስትዮሽ ድርድሩ ህብረቱ ከፍተኛ ሚና እንደሚጫወት ተስፋ አለን አሉ፡፡ አቶ ደመቀ “ለአፍሪካ ችግሮች አፍሪካዊ መፍትሔ” መርህ መሰረት የሶስትዮሽ ድርድሩ ውጤታማ እንዲሆን የአፍሪካ ህብረት ሚናው አጠናክሮ እደሚቀጥል ያላቸውን እምነት ገልጸዋል።አቶ ደመቀ የግድቡ ሁለተኛ ዙር የውኃ ሙሊት በተያዘለት ጊዜ እንደኪካሄድም አብራርተዋል፡፡ አቶ ደመቀ […]

ኢትዮጵያውያን የውጭ ጣልቃ ገብነትን በመቃወም በያሉበት ሆነው ድምጻቸውን የሚያሰሙበት መርሃ ግብር ዛሬ ይካሄዳል::

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 14፣ 2013 ኢትዮጵያውያን የውጭ ጣልቃ ገብነትን በመቃወም በያሉበት ሆነው ድምጻቸውን የሚያሰሙበት መርሃ ግብር ዛሬ ይካሄዳል:: በፕሮግራሙ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን የውጭ አገራትን ጣልቃ ገብነት በመቃወም እጃችሁን ከኢትዮጵያ ላይ አንሱ" በሚል መሪ ሐሳብ በያሉበት ሆነው ለአንድ ሰዓት መልዕክታቸውን ያስተላልፋሉ፡፡ ከመልእክት ከማስተላለፊያ መንገዶች አንዱ ጣልቃ ገብነቱን የሚቃወም የዲጂታል ፊርማ ማሰባሰብ መሆኑም ታውቋል፡፡ መርሃ-ግብሩ ብሔራዊ […]

የሩሲያው ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን ማንኛውም ኃይል ከሩሲያ ግዛት ቅንጣት መሬት ለመውሰድ ቢሞክር፣ “ጥርሱን እናራግፍለታለን” ሲሉ አስጠነቀቁ።

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 14፣ 2013 የሩሲያው ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን ማንኛውም ኃይል ከሩሲያ ግዛት ቅንጣት መሬት ለመውሰድ ቢሞክር፣ “ጥርሱን እናራግፍለታለን” ሲሉ አስጠነቀቁ። ፕሬዚዳንቱ ከከፍተኛ ባለሥልጣኖቻቸው ጋር ባደረጉት የቪዲዮ ስብሰባ በተናገሩትና በቴሌቪዥን በተላለፈው ንግግራቸው፣ አንዳንድ የውጭ ሃገራት በከርሰ-ምድር ሃብት የበለፀገውን ሳይቤሪያ የተባለውን የሩሲያን ግዛት አስመልክቶ ከሚሰጡት አስተያያት ተነስተው መሆኑን ገልፀዋል። ከውጭ ሃገራት ተነገሩ የተባሉት ነገሮች በቀድሞዋ […]

ከግንቦት ወር አጋማሽ ጀምሮ የክረምት ዝናብ በተወሰኑ የኢትዮጵያ ክፍሎች ተፅዕኖ እንደሚኖረው ተገለጸ::

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 14፣ 2013  ከግንቦት ወር አጋማሽ ጀምሮ የክረምት ዝናብ በተወሰኑ የኢትዮጵያ ክፍሎች ተፅዕኖ እንደሚኖረው ተገለጸ:: የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር አቶ አህመዲን አብዱልከሪም ከግንቦት ወር አጋማሽ ጀምሮ የክረምቱ ዝናብ ተፅዕኖ ሊበረታ ስለሚችል በአርሶና አርብቶ አደር አካባቢዎች ጉዳት ሊያስከትል ስለሚችል ጥንቃቄ ሊደረግ ይገባል ብለዋል። ከግንቦት ወር አጋማሽ ጀምሮ የክረምት ዝናብ ተፅዕኖው ሊጀምር እንደሚችል የጠቆሙት አቶ […]

መንግሰት ስለ ኬሚካል ጦር መሳሪያዉ የሰጠዉ ምላሽ::

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 16፣ 2013 የኢትዮጵያ መንግስት በትግራይ ክልል የኬሚካል ጦር መሳሪያ ተጠቅሟል የሚለውን ዘገባ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስተባበለ፡፡የውጭ ጉዳይ  ሚኒስቴር ሁኔታውን አስመልክቶ ባወጣው መግለጫ በቴሌግራፍ መፅሄት ላይ ታትሞ የወጣውን በትግራይ ክልል ከጦር ወንጀል የማይተናነስ ድርጊት መፈፀሙን የሚያመላክት ሪፖርት አጥብቆ እንደሚቃወም ገልጿል፡፡ በመፅሄቱ የአፍሪካ ዘጋቢ  የሆነው ዊል ብራውን መቀመጫውን ናይሮቢ ላደረገው የቴሌግራፍ መፅሄት ባጠናቀረው […]