loading
ብራዚል ኮሮናቫይረስ ከቁጥጥሬ ውጭ አይደለም ብትልም በቀን ውስጥ የሚመዘገበው የሟችና የታማሚ ቁጥር እያሻቀበ ነው::

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 10 ፣ 2012  ብራዚል ኮሮናቫይረስ ከቁጥጥሬ ውጭ አይደለም ብትልም በቀን ውስጥ የሚመዘገበው የሟችና የታማሚ ቁጥር እያሻቀበ ነው:: የፕሬዚዳት ዣየር ቦልሶናሮ የፅህፈት ቤት ሀላፊ ዋልተር ብራጋ ኔቶ በሰጡት መግለጫ በሀገራችን ኮቪድ 19 ቀውስ ፈጥሮብናል ግን ደግሞ ከቁጥጥራችን አልወጣም ማለታቸው ብዙዎቹን አስገርሟል ነው የተባለው፡፡ ምክንያቱም ሀላፊው ይህን አይነት መግለጫ የሰጡት በብራዚል በ24 በሰዓታት […]

የኢትዮጵያ ወንጌላዊት መካነ-ኢየሱስ ቤተክርስቲያን ከሁለት ሚሊዮን ብር በላይ በሚሆን ግምት የምግብና የንፅህና መጠበቂያ ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገች፡፡

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 10 ፣ 2012  የኢትዮጵያ ወንጌላዊት መካነ-ኢየሱስ ቤተክርስቲያን ከሁለት ሚሊዮን ብር በላይ በሚሆን ግምት የምግብና የንፅህና መጠበቂያ ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገች፡፡ ቤተክርስትያንዋ ላደረገችዉ ድጋፍ በአማራ እና አፋር ክልል በኮቪድ-19 ወረርሺኝ ሳቢያ ለችግር ለተጋለጡ 10 ሺህ ለሚሆኑ ሰዎች የሚሰራጭ ነዉ፡፡ ለደቡብ ወሎ ዞን የተደረገውን 800 ሺህ ብር በሚጠጋ ወጪ የሙቀት መለኪያ፣የምግብ ዘይት፣ዱቄትና የተለያዩ የንፅህና […]

 በፌደሬሽን ም/ቤት ፤በህግ ትርጉም ሽፋን የተላለፈዉን የፖለቲካ ዉሳኔ እንደሚቃወም ባልደራስ ለእዉነተኛ ዲሞክራሲ ገለጸ::

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 10 ፣ 2012 በፌደሬሽን ም/ቤት ፤በህግ ትርጉም ሽፋን የተላለፈዉን የፖለቲካ ዉሳኔ እንደሚቃወም ባልደራስ ለእዉነተኛ ዲሞክራሲ ገለጸ::ፓርቲዉ ለአርትስ ባለከዉ መግለጫ እንዳስታወቀዉ ፤የፌደሬሽን ምክርቤት በሰኔ 3 ቀን 2012 ዓ/ም ባደረገዉ ስብሰባ ፤6ኛዉ አገራዊ እና ክልላዊ ምርጫ በዉል ላልታወቀ ዘመን እንዲራዘም እና እድሜያቸዉ መስከረም 30 ቀን 2012 ዓ/ም የሚያበቃላቸዉ ሁሉም ም/ቤቶች በስልጣናቸዉ እንዲቀጥሉ መወሰኑ አግባብንት […]

የአረንጓዴ ዐሻራ አላማ የለም አፈር መሸርሸርን ማስቀረት መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ተናገሩ::

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 10 ፣ 2012  የአረንጓዴ ዐሻራ አላማ የለም አፈር መሸርሸርን ማስቀረት መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ተናገሩ::ጠቅላይ ሚኒስትሩ በፌስቡክ ገፃቸው ላይ እንዳሰፈሩት የአረንጓዴ ዐሻራ አላማ የለም አፈር መሸርሸርን ማስቀረት መሆኑን ገልጸዋል፡፡የደን ምንጣሮ እና የአየር ንብረት ለውጥ ከሌሎች መንሥኤዎች ጋር ተዳምረው በየዓመቱ በኢትዮጵያ የለም አፈር መሸርሸርን ያስከትላሉ ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ።የአረንጓዴ ዐሻራ አንዱ ግብ […]

በሴቶችና ህጻናት ላይ እየደረሰ ያለውን ጥቃት ለመከላከል የሚደረገው ጥረት ትኩረት ሊሰጠዉ ይገባል ተባለ::

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 10 ፣ 2012  በሴቶችና ህጻናት ላይ እየደረሰ ያለውን ጥቃት ለመከላከል የሚደረገው ጥረት ትኩረት ሊሰጠዉ ይገባል ተባለ::በሴቶችና ህጻናት ላይ እየደረሰ ያለውን ጥቃት በማስመልከት የተቀናጀ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በመስጠት ላይ በሚገኙ ተቋማት በመገኘት ወ/ሮ አዳነች አቤቤ እንደገለጹት :: ፤የኮቪድ 19 ወረርሺኝን ለመከላከል ከፍተኛ ርብርብ እየተደረገ ባለበት በዚህ ወቅት ትኩረታችን የቁጥር ጉዳይ ሳይሆን አንድም […]

የአውሮፓ ፓርላማ በሚቀጥለው ሳምንት በዘረኝነት ጉዳይ ላይ ያተኮረ ውይይት ላደርግ ነው አለ፡፡

የጥቁር አሜሪካዊውን ጆርጅ ፍሎይድን ግድያ ተከትሎ በርካታ ሀገራ እና ተቋማት በጉዳዩ ላይ ትልቅ ትኩረት ሰጥው መወያያት ከጀመሩ ሰነባብተዋል፡፡ ህብረቱ በጥቁሮች ላይ የሚደርሰው ጫና እንዲቆም የሚያደርግ አሰራር ለመዘርጋት እና የዘር መድሎ የሚያደርጉ ግለሰቦችና ቡደኖችን የሚያወግዝ ውይይት ያደርጋል ተብሎ ይጠበቃል፡፡ ዩሮ ኒውስ እንደዘገበው በአውሮፓ ህብረት ቁልፍ የሚባሉ ስራዎች የተያዙት ነጭ ቀለም ባላቸው ግለሰቦች ሲሆን ከተመሰረተ ከ60 ዓመታት […]

ህዳሴው ግድብ ላይ የሚደረገው ድርድርድር ከቴክኒክ አንፃር መሰረታዊ የተባሉ ጉዳዮች ቢፈቱም ሙሉ ስምምነት ሆኖ ለመውጣት የሚቀረው ጉዳይ እንዳለ ተገለፀ::

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 11 ፣ 2012 ህዳሴው ግድብ ላይ የሚደረገው ድርድርድር ከቴክኒክ አንፃር መሰረታዊ የተባሉ ጉዳዮች ቢፈቱም ሙሉ ስምምነት ሆኖ ለመውጣት የሚቀረው ጉዳይ እንዳለ ተገለፀ:: በመጀመርያ የውሃ ሙሌትና አመታዊ ስራ ላይ ትኩረቱን አድርጎ በኢትዮጵያ በሱዳንና ግብፅ መካከል በቪዲዮ በመታገዝ እየተካሄደ ያለው ድርድር ለሰባተኛ ቀን ትላንት ተካሂዷል።የኢፌዴሪ የውሃ፣ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስቴር እንዳለው ከሚኒስትሮቹ ውይይት ቀደም […]

በኮሮና ዙርያ የተሰሩ ከ20 በላይ ጥናቶች በኦን ላይን ኮንፈረንስ ለውይይት በመቅረብ ላይ ናቸው ።

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 11 ፣ 2012 በኮሮና ዙርያ የተሰሩ ከ20 በላይ ጥናቶች በኦን ላይን ኮንፈረንስ ለውይይት በመቅረብ ላይ ናቸው ።የኦንላይን ኮንፍረንሱ ምሁራን በኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ዙሪያ ያከናወኑዋቸው ጥናቶች ለማሳወቅና ቫይረሱን አስመልክቶ የእውቀት ሽግግር ለማድረግ ያለመ ነው ብለዋል።ውይይቱ ላይ የመቐለ አዲስ አበባ ፣ ባህርዳር እና ሃረማያ ዩኒቨርሲቲዎች ምሁራን የተሳተፉበት መሆኑን ዶክተር አዲሱ ተናግረዋል ።ጥናታዊ ጽሁፎቹ […]

በአፍሪካ ህብረት የፓን አፍሪካ የእንስሳት ክትባት ማዕከል የኮሮቫይረስን ለመከላከል የሚያደርገውን የምርምር ስራ እንደሚደግፍ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ገለጸ።

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 11 ፣ 2012 በአፍሪካ ህብረት የፓን አፍሪካ የእንስሳት ክትባት ማዕከል የኮሮቫይረስን ለመከላከል የሚያደርገውን የምርምር ስራ እንደሚደግፍ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ገለጸ።የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዶክተር አብርሃም በላይ በቢሾፍቱ ከተማ የሚገኙትን የአፍሪካ ህብረት የፓን አፍሪካ የእንስሳት ክትባት ማዕከልና ብሄራዊ የእንስሳት ህክምና ኢንስቲትዩት ዛሬ ጎብኝተዋል።የፓን አፍሪካ የእንስሳት ክትባት ማዕከል በክትባትና መድሃኒት ምርቶች ላይ የሚደረገውን ቁጥጥርና […]

በኮሮና ቫይረስ ምክንያት የሚከሰትን የደም አቅርቦት እጥረት ለመቅረፍ የምስራቅ ወለጋ ዞን አመራሮች ደም ለገሱ፡፡

የዞኑ ኮሚኒኬሽን ለአርትስ በላከዉ መግለጫ እንዳስታወቀዉ ቀደም ሲል የጤና ሚኒስቴርና የኢትዮጵያ ብሔራዊ የደም ባንክ አገልግሎት በኮሮና ቫይረስ ምክንያት አገራዊ የደም አቅርቦት በመቀነሱ የልገሳ ጥሪ ማቅረቡን ተከትሎ ነዉ ፡፡ በልገሳ መረሓ ግብሩ የተገኙት የምስራቅ ወለጋ ዞን አስተዳዳሪ አቶ አስመራ ኢጃራ በሰጡት አስተያየት፤ የኮሮናቫይረስ ከመግባቱ በፊት ሲቀርብ የነበረው ደም በመቀነሱ በችግር ጊዜ ሕዝብና አገርን የማሻገር ሃላፊነታችንን እንወጣለን […]