loading
አንካራና ዋሽንግተን ብድር በመመላለስ የንግድ ጦርነቱን አጧጡፈውታል፡፡

ቱርክ በአሜሪካ ምርቶች ላይ እስከ 140 በመቶ የሚሆን ታሪፍ ጣለች፡፡ ፕሬዝዳንት ረሲፕ ጣይብ ኤርዶሀን አሜሪካ በሀገሬ ላይ ያወጀቸው ኢኮኖሚያዊ ጥቃት መልስ ያስፈልገዋል ሲሉም ተደምጠዋል፡ ኤርዶሀን ባለፈው ሰኞ በሰጡት መግለጫ ከእንግዲህ ከአሜሪካ የሚገቡ የኤሌክትኒክስ ምርቶች በቱርክ ገበያ ቦታ የላቸውም ብለው ነበር፡፡ አልጀዚራ እንደዘገበው የቱርክ መንግስት በአሜሪካ ምርቶች ላይ ሌላ ተጨማሪ ታሪፍ ጥሏል፡ በዚህም መሰረት የሲጋራ ምርቶች […]

ሙን ጃይ ኢን ደቡብና ሰሜን ኮሪያን በፍቅር ሀዲድ ሊያገናኙ ያስባሉ፡፡

የደቡብ ኮርያው ፕሬዝዳንት ለዓመታት በግጭት ውስጥ የቆዩትን ሴኡልና ፒዮንግያንግን የሚያገናኝ የባቡር መስመር ግንባታ ለማካሄድ እቅድ ይዘዋል፡፡ ምንም እንኳ በደቡብና ሰሜን ኮርያ መካከል የፖለቲካ ውህደት ለማድረግ ጊዜ የሚፈልግ ጉዳይ ቢሆንም በትራንስፖርት ቢተሳሰሩ ኢኮኖሚያቸውን ከማሳደግ አልፈው የሁለቱ ሀገራት ህዝቦች እርስ በርስ እንዲቀራረቡ በር ይከፍታል ብለዋል ሙን ጃይ ኢን፡፡ አልጀዚራ እንደዘገበው ፕሬዝዳንቱ ተግባራዊ እንዲሆን ያሰቡት “ሬይልሮድ ኮሚዩኒቲ” የተሰኘው […]

ለስደተኞች ስራ በማትሰጠው ለንደን ወጣቱ ሲቪውን ይዞ ጎዳና ላይ ለመቆም ተገዷል ፡፡

ሞሀመድ ኤልባራዲ ይባላል፡፡ የ22 ዓመት ወጣት ነው፡፡ ከሊቢያ ተሰዶ መኖሪያውን ለንደን ያደረገው ኤልባራዲ ከለንደን ዩንቨርሲቲ ኮሌጅ በኤሮስፔስ ሳይንስ በማስተርስ ዲግሪ ተመርቋል፡፡ ሆኖም ከ70 በላይ በሚሆኑ ቀጣሪ ድርጅቶች ውስጥ የስራ ማመልከቻ ቢያስገባም አንዳቸውም ምላሽ አልሰጡትም፡፡ በዚህ ሁኔታ የተማረረው ኤልባራዲ ታዲያ በመጨረሻ አንድ ሀሳብ መጣለት፡፡ ስራ እንደሚፈልግ የሚጠቁም ማስታወቂያ ይዞ ሰው በሚበዛበት አካባቢ መቆም፡፡ እናም ይህ ወጣት […]

በህንድ በተከሰተ የጎርፍ አደጋ ከመቶ በላይ ሰዎች ሲሞቱ በሺዎች ሚቆጠሩት ደግሞ ከቤት ንብረታቸው ተፈናቅለዋል ፡፡

በህንድ በተከሰተ የጎርፍ አደጋ ከመቶ በላይ ሰዎች ሲሞቱ በሺዎች ሚቆጠሩት ደግሞ ከቤት ንብረታቸው ተፈናቅለዋል ፡፡ ቢቢሲ እንደዘገበው የህንዷ ኬራላ ግዛት ህንድን በክፍለ ዘመኑ ካጋጠማት አስከፊውን የጎርፍ አደጋ አስተናግዳለች፡፡ የግዛቷ ባለስልጣናት እንደተናገሩት በአደጋው ሳቢያ 164 ሰዎች ህይወታቸው አልፏል፡፡ ከሟቾቹ በተጨማሪም ቁጥራቸው ወደ 23 ሺህ የሚጠጋ ነዋሪዎች ቤት አልባ ሆነዋል፡፡ ባለስልጣናቱ ነዋሪዎቹ በፍጥነት የአደጋውን አካባቢ ለቀው እንዲወጡም […]

ህንድ ባጋጠማት የጎርፍ አደጋ የሟቾችና የተፈናቃዮች ቁጥር ጨምሯል፡፡

ህንድ ባጋጠማት የጎርፍ አደጋ የሟቾችና የተፈናቃዮች ቁጥር ጨምሯል፡፡ በክፍለ ዘመኑ አስከፊ የተባለለት ጎየርፍ አደጋ ያጋጠማት ህንድ 350 ዜጎቿ ለህልፈት ሲዳረጉ ከ800 ሽህ በላይ የሚሆኑት ደግሞ ቤት ንብረታቸውን ጥለው ተፈናቅለዋል፡፡ አልጀዚራ እንደዘገበው ኬራላ በተባለችው የደቡባዊ ህንድ ግዛት የጣለው ከባድ ዝናብ ባስከተለው ጎርፍ ህይዎታቸው አደጋ ላይ ያሉ ዜጎችን ለመታደግ የአደጋ ጊዜ ሰራተኞች አሁንም ጥረታቸውን ቀጥለዋል፡፡ በግዛቷ የሚገኙ […]

የኒውዮርክ ፍርድ ቤት የቀድሞውን የትራምፕን ጠበቃ ጥፋተኛ ብሏቸዋል፡፡

የቀድሞው የፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ጠበቃ የነበሩት ሚካኤል ኮሆን ጥፋተኛ የተባሉት በ2016ቱ ምርጫ ለቅስቀሳ ከተመደበው ገንዘብ ህጉ ከሚፈቅደው ውጭ ክፍያ እንዲፈጸም አድርገዋል ተብለው ነው፡፡ ኮሆን በበኩላቸው ድርጊቱን መፈጸማቸውን አምነው ነገር ግን ይህን ያደረኩት ፕሬዝዳንቱ አዘውኝ ነው ብለዋል፡፡ ቢቢሲ እንደዘገበው የሚካኤል ኮሆን ጠበቃ ይህ ክፍያ ደንበኛየን ኮሆንን ወንወጀለኛ ካስባለ ለምን ፕሬዝዳንት ትራምፕን አያስጠይቅም ሲሉ ፍርድ ቤቱን ጠይቀዋል፡፡ […]

የአሜሪካ መንግስት ልኡካን በኢትዮጵያ ጉብኝት ለማድረግ በዛሬው እለት አዲስ አበባ ይገባሉ።

በሪፐብሊካን ኮንግረስማን ክሪስቶፈር ስሚዝ የሚመራው የልኡካን ቡድን በኢትዮጵያ እየመጡ ባሉ ለውጦች ዙሪያ ከኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አበይ አህመድ እና ከውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዶክተር ወርቅነህ ገበየሁ ጋር ተገናኝተው እንደሚወያይም ይጠበቃል። የልኡኩ መሪ ኮንግረስማን ክርስቶፈር ስሚዝ ከአሜሪካ ድምፅ (ቪኦኤ) ራዲዮ ጋር ባደረጉት ቆይታ፥ በኢትዮጵያ በሚኖራቸው ቆይታ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ እና ከውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዶክተር ወረቅነህ ጋር […]

የአሜሪካና የቻይና የንግድ ጦርነት ተባብሷል፡፡

ሲጂቲኤን እንደዘገበው ሁለቱ ሀገሮች ብድር እየተመላለሱ አንዱ በሌላው ላይ የታሪፍ ጭማሪ መቀጠሉን ተያይዘውታል፡፡ አሁን አሜሪካ በቻይና ምርቶች ላይ የ25 በመቶ የታሪፍ ጭማሪ መጣሏን ተከትሎ ቻይናም በብርሃን ፍጥነት በዋሽንግተን ምርቶች ላይ ተመሳሳይ ታሪፍ ጥላባቸዋለች፡፡ አሜሪካ የ25 በመቶ ታሪፍ የጣለችው ከቻይና ወደ ሀገሯ በሚገቡ የኤሌክትሮኒክስ፣ የፕላስቲክ፣ የባቡር መገጣጠሚያ መሳሪያዎችና የኬሚካል ውጤቶች ላይ ሲሆን ቻይና በአጸፋው በተሸከርካሪዎች፣ በኢነርጂና […]

ቴል አቪቭ ከዋሽንግተን ሌላ ውለታ እየጠበቀች ነው፡፡

የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚንስትር ቤናሚን ኔታናያሁ እራኤል ከሶሪያ በሀይል የወሰደችውን የጎላን ተራራን የባለቤትነት እውቅና እንድትሰጣት አሜሪካን አጥብቀው ጠይቀዋል፡፡ ከአሁን ቀደም እየሩሳሌም የእስራኤል ዋና ከተማ ናት የሚለውን ውሳኔ ያሳለፈው የትራምፕ አስተዳደር አሁን ደግሞ ለጎላን ተራራ ሌላ እውቅና እንዲሰጠን የምንችለውን ሁሉ እናደርጋለን ብላል ኔታናያሁ፡፡ ኔታናያሁ ይህን ያሉት የአሜሪካው የደህንነት አማካሪ ጆን ቦልተን ሀገራቸው እስካሁን የጎላን ተራራ ለእስራኤል ይገባታል […]

ህንድ የአቡዳቢን እርዳታ አልፍልግም አለች፡፡

የተባበሩት አረብ ኤሜሬቶች ህንድ ያጋጠማትን የጎርፍ አደጋ ተከትሎ 100 ሚሊዮን ዶላር የድጋፍ ገንዘብ ለመለገስ ተዘጋጂታ ነበር፡፡ ይሁን እንጂ ህንድ ምንም እንኳ በአደጋው 400 ዜጎቿ ህይዎታቸውን ቢያጡና በሚሊዮን የሚቆጠሩት ቢፈናቀሉባትም እርዳታውን አልቀበልም ብላለች፡፡ የህንድ የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት በሰጠው መግለጫ እንዳሳታወቀው የሀገሪቱ ፖሊሲ እንዲህ ዓይነት የተፈጥሮ አደጋ ባጋጠመ ጊዜ የመልሶ ማቋቋሙን ሰስራ በራሷ አቅም እንድትወጣው ስለሚያስገድድ […]