loading
በአፍሪካ ህብረት የፓን አፍሪካ የእንስሳት ክትባት ማዕከል የኮሮቫይረስን ለመከላከል የሚያደርገውን የምርምር ስራ እንደሚደግፍ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ገለጸ።

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 11 ፣ 2012 በአፍሪካ ህብረት የፓን አፍሪካ የእንስሳት ክትባት ማዕከል የኮሮቫይረስን ለመከላከል የሚያደርገውን የምርምር ስራ እንደሚደግፍ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ገለጸ።የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዶክተር አብርሃም በላይ በቢሾፍቱ ከተማ የሚገኙትን የአፍሪካ ህብረት የፓን አፍሪካ የእንስሳት ክትባት ማዕከልና ብሄራዊ የእንስሳት ህክምና ኢንስቲትዩት ዛሬ ጎብኝተዋል።የፓን አፍሪካ የእንስሳት ክትባት ማዕከል በክትባትና መድሃኒት ምርቶች ላይ የሚደረገውን ቁጥጥርና የምርምር ስራ በጋራ ለማከናወን ስምምነት መድረሳቸው ይታወቃል።ሚኒስትሩ ዶክተር አብርሃም በላይ እንዳሉት ማዕከሉ የኮሮቫይረስን ለመከላከል የሚያደርገውን የምርምር ስራ እንደገፋለን ብለዋል።

ለጥናትና ምርምር ስራዎች በቴክኖሎጂ የታገዙ መፈትሄዎችን በመጠቀም የምርምር ስራዎችን ውጤታ ለማድረግ እንደሚሰራም ገልጸዋል።ለማዕከሉ የሚደረገው ድጋፍና ክትትልም ቀጣትነት እንደሚኖረው ሚኒስቴሩ ጠቁመዋል።ማዕከሉ ኮሮናቫይረስ ወረርሽኝን ተጽዕኖ ለመቋቋምና ለመቆጣጠር በምርምርና ፈጠራ የታገዘ መፍትሄ ለማምጣት እንደሚሰራ ተገልጿል።የሃገር በቀል እጽዋት በመውሰድ የቤተ ሙከራ ሂደቶችን በተሟላ ሁኔታ ለማከናወን እንደሚችል የማዕከሉ ዳይሬክተር ዶክትር ኒክ ንዋንክፓ ገለፃ አድርገዋል ተብሏል።

Write a Reply or Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *