loading
ትራምፕ የዓለም ሙቀት መጨመር አያሳስበኝም አሉ

አርትስ 18/03/2011

 

ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ይህን ያሉት የአየር ንብረት ለውጥን የተመለከተ ሪፖርት ከቀረበላቸው በኋላ ነው፡፡

የአሜሪካ ብሄራዊ የአየር ንብረት ለውጥ ጥናት ተቋም በሀገሪቱ እየተባባሰ የመጣው የተፈጥሮ አደጋ በዓለም ሙቀት መጨመር ሳቢያ መሆኑን ይፋ ቢያደርግም ትራምፕ ግን እኔን አያሳስበኝም ብለዋል፡፡

ሪፖርቱን አይቸዋለሁ የተወሰነውንም አንብቤዋለሁ ግን ከማጭበርበር የዘለለ እውነትነት የለውም ነው ያሉት ፕሬዝዳንቱ፡፡

በሀይል ማመንጫዎች እና በተሽከርካሪዎች የሚፈጠረው የጋዝ ብክለት በዚሁ ከቀጠለ በአሜሪካ ችግሩን ለመቋቋም በየዓመቱ 155 ቢሊዮን ዶላር የሚተመን የጉልበት ወጭ ይጠይቃል፡፡

እንዲሁም የባህር ዳርቻዎችን ከብክለት ለመታደግ 118 ቢሊዮን ዶላር ዓመታዊ ኪሳራ እንደሚደርስባት ሪፖርቱ በግልፅ አስቀምጧል፡፡

ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከዓለም አቀፉ የአየር ንብረት ለውጥ ስምምነት ሀገራቸውን ከማስወጣታቸውም በላይ በገዛ ባለ ስልጣኖቻቸው ላይ እምነት አለማሳደራቸውም እያሰተቻቸው ነው፡፡

Write a Reply or Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *