loading
በስፔን ኮፓ ዴል ሬይ ባርሴሎና ሽንፈት ገጥሞታል

በስፔን ኮፓ ዴል ሬይ ባርሴሎና ሽንፈት ገጥሞታል

የካታላኑ ባርሴሎና በስፔን የንጉስ ዋንጫ የሩብ ፍፃሜ የመጀመሪያ ጨዋታ ለማድረግ ወደ ራሞን ሳንቼዝ ፒዡዋን አቅንቶ በሲቪያ የ2 ለ 0 ሽንፈት አስተናግዶ ተመልሷል፡፡

በሙሉ ጨዋታው አምበሉ ሊዮኔል ሜሲ ባርሳን ያላገለገለ ሲሆን አዲሱ ፈራሚ ኬቨን ፕሪንስ ቦአቲንግ ለቡድኑ የመጀመሪያ ጨዋታውን ማድረግ ቢችልም በሁለተኛው አጋማሽ በሊዩስ ሱሬዝ ተቀይሮ እስከጣበት ጊዜ ድረስ ማራኪ እንቅስቃሴ ማሳየት አልቻለም፡፡

በጨዋታው የመጀመሪያ አጋማሽ ግብ ያልተስተናገደ ሲሆን በሁለተኛው አጋማሽ ግን ፓብሎ ሳራቢያ እና ዊሳም ቤን ያድር ያስቆጠሯቸው ሁለት ጎሎች የአንዳሉዥያውን ቡድን አሸናፊ አድርገውታል፡፡

የአራት ዓመት የኮፓ ዴል ሬይ የበላይነቱ አደጋ ላይ የወደቀው ባርሳ፤ በመልሱ ግጥሚያ ካምፕ ኑ ላይ በሰፊ የግብ ልዩነት መሸነፍ ግድ ሁኖበታል፡፡

ዛሬ ምሽት ሁለት የግማሽ ፍፃሜ የመጀመሪያ ዙር ፍልሚያዎች ሲካሄዱ 5፡30 ሲል ሪያል ማድሪድ በሳንቲያጎ ቤርናባው ጅሮናን ያስተናግዳል፡፡ ኢስፓኞል ደግሞ ከሪያል ቤቲስ ይጫወታሉ፡፡

Write a Reply or Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *