loading
በባንክ ብድር ለእርሻ የተገዙ ማሽኖችን ማከራየት ተፈቀደ

አርትስ 29/02/2011

 

የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ለዘመናዊ እርሻ በብድር የተገዙ ማሽኖች ለሶስተኛ ወገን እንዲከራዩ ፈቀደ።

ባንኩ ከዚህ ቀደም የደነገገውን ማሽኖችን ለሶስተኛ ወገን የማከራየት ክልከላ አንስቷል።

እዚህ ውሳኔ ላይ የደረሰው ማሽን ለመግዛት ብድር የወሰዱ ሰዎች በሂደት ገንዘቡን ከታቀደለት አላማ ውጭ መጠቀምበመጀመራቸው ነው ተብሏል።

በዚህም ተበዳሪዎች የሚፈልጉትን ማሽን ገዝቶ በማቅረብ ተገልጋዮቹ በኪራይ እንዲጠቀሙበት የሚያስችለውን የሊዝፋይናንሲንግ አገልግሎት መጀመሩን አስታውቋል።

ይህ አሰራር ተበዳሪዎች የተከራዩትን ማሽን ሙሉ ዋጋ ከከፈሉ በኋላ ማሽኑ የራሳቸው ንብረት ሆኖ የሚቀርበት አሰራርነው።

ባንኩ አስፈላጊውን መስፈርት ያሟሉ ግለሰቦች በመምጣት ማሽኖችን በብድር ገዝተው ማከራየት የሚችሉ መሆኑንም ጨምሮ ተናግሯል።

Write a Reply or Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *