loading
ቦርዱ የመራጮች ትምህርት ማስተማር ለሚፈልጉ ሲቪል ማህበራት የእውቅና ፍቃድ የመስጫ ግዜን አራዘመ፡፡

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 15፣ 2012 ቦርዱ የመራጮች ትምህርት ማስተማር ለሚፈልጉ ሲቪል ማህበራት የእውቅና ፍቃድ የመስጫ ግዜን አራዘመ፡፡

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ እንዳስታወቀዉ ለመራጮች ትምህርት ማስተማር ለሚፈልጉ ሲቪል ማህበራት   ለቦረድ ማመልከቻዎችን ማቅረቢያ የጊዜ ገደብ የሚጠናቀቀው መጋቢት 11 ቀን 2012 ዓ.ም እንደነበረ አስታዉሶ፡፡

ነገር ግን ቦርዱ ተጨማሪ የምዝገባ ቀናት አስፈላጊነትን ከግምት ውስጥ በማስገባት የማመልከቻ ማስገቢያው የጊዜ ገደብ እስከ የፊታችን አርብ መጋቢት 18 ቀን 2012 ድረስ ያራዘመ መሆኑን ገልጿል፡፡

ቦርዱ የመራጮች ትምህርት ለመስጠት የእውቅና ፍቃድ መውሰድ የሚፈልጉ እና መስፈርቱን የሚያሟሉ ሲቪል ማህበራት በተገለጸው የጊዜ ገደብ ውስጥ ማመልከት የምትችሉ መሆኑን ገልጿል፡፡

Write a Reply or Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *