loading
አዲስ አበባ በኳታር ፋውንዴሽን የኩላሊት ህክምና ማዕከል ይገነባላታል ተባለ

አዲስ አበባ በኳታር ፋውንዴሽን የኩላሊት ህክምና ማዕከል ይገነባላታል ተባለ

አርትስ 04/04/2011

 የጤና ጥበቃ ሚኒስትሩ ዶክተር አሚር አማን የኳታር ፋውንዴሽን በአዲስ አበባ ከተማ የኩላሊት ህክምና አገልግሎትን ብቻ የሚሰጥ ማዕከል ለመገንባት በኢትዮጵያ ከኳታር አምባሳደር ሀማድ አል – ዶሳሪ ጋር ተስማምተናል ሲሉ በፌስቡክ ገፃቸው አስፍረዋል።

ዶክተር አሚር አማን ስምምነት ላይ የደረሱት ከአምባሳደር ሀማድ አል-ዶሳሪ ጋር ከተወያዩ በኋላ መሆኑን አስታውቀዋል፡፡

ሚኒስትሩ ትናንት ሁሉን ዓቀፍ የጤና ተደራሽነት ቀን መሆኑን አስታውሰው፥ የሰው ልጅ ያለምንም ልዩነትና የፋይናንስ ችግር የሚያስፈልገውን መሰረታዊ ጤና አገልግሎት የማግኘት መብት እንዳለው በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው አስታውቀዋል፡፡

Write a Reply or Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *