loading
ኢትዮጵያ በ72 ኛው የጤና አለም አቀፍ ጉባኤ ላይ እየተሳተፈች ነዉ፡፡

ኢትዮጵያ በ72 ኛው የጤና አለም አቀፍ ጉባኤ ላይ እየተሳተፈች ነዉ፡፡

የጤና ሚኒስትሩ  ዶክተር አሚር አማን በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው እንደገለፁት የኢትዮጵያ ልዑካን ቡድን በጄኔቫ ስዊዘርላንድ እየተካሄደ ባለው 72ተኛው የጤና አለም አቀፍ ጉባዔ ላይ ኢትዮጵያ ሁለት አዳዲስ ለውሳኔ የሚቀርቡ ሀሳቦችን ታቀርባለች፡፡

ኢትጵያ ከዚሁ ጋር ተያይዞ ሁለት ጎን ለጎን የሚካሄዱ ስብሰባዎችን በማዘጋጀት የምትመራ እንደሆነም ተነግሯል፡፡

የልዑካኑ ቡድኑ ከሌሎች ሀገራት ጋር የልምድ ልውውጥ እና አዳዲስ ትብብሮችን ለመፍጠር ከተለያዩ አጋር ድርጅቶች ጋር ውይይት እንደሚያደርግም ዶክተር አሚር አማን አስታዉቀዋል፡፡

 

Write a Reply or Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *