loading
ከንቲባ ታከለ ኡማ በመዲናችን አዲስ አበባ ከሚኖሩ የሶማሌ ማህበረሰብ አባላት ጋር ተወያዩ። 

ከንቲባ ታከለ ኡማ በመዲናችን አዲስ አበባ ከሚኖሩ የሶማሌ ማህበረሰብ አባላት ጋር ተወያዩ።

የከተማ አስተዳደሩ ተቀዳሚ ተግባር የከተማውን ነዋሪ ህይወት መቀየር መሆኑን የገለፁት ኢ/ር ታከለ ኡማ የሶማሌ ማህበረሰብም የዚሁ አካል መሆናቸውን ጠቁመዋል፡፡

በአዲስ አበባ ውስጥ የሚኖሩ ከ30ሺ በላይ የሚሆኑ የሶማሌ ማህበረሰብ አባላትም እንደ ከተማ ነዋሪነታቸው የስራ ዕድል ተጠቃሚ ፣ የጋራ መኖሪያ ቤቶች ዕድል እና የመንግስት አገልግሎቶች ተጠቃሚ እንዲሆኑ የከተማ አስተዳደሩ እንደሚሰራም ኢ/ር ታከለ ኡማ ቃል ገብተዋል።

የመድረኩ ተሳታፊዎችም ከከተማ አስተዳደሩ ጋር ተቀራርቦ በጋራ ለመስራት ዝግጁ መሆናቸውን ገልፀዋል፡፡

በመድረኩ ላይ ከፍተኛ የኦብነግ አመራሮች፣ የጎሳ መሪዎች እና በርካታ የማህበረሰቡ አባላት ተሳትፈዋል፡፡

 

Write a Reply or Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *