loading
ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ለሰላም በሚል መሪ ቃል ኮንፈረንስ ተካሄደ።

ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ለሰላም በሚል መሪ ቃል ኮንፈረንስ ተካሄደ።
በከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የመጀመሪያው የሰላም ኮንፈረንስ ዛሬ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ተካሂዷል።
”ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ለሰላም” በሚል መሪ ቃል በተካሄደው ኮንፍረንስ ላይ ከሁሉም ዩኒቨርስቲዎች የተወከሉ የአስተዳደር አካላትና ተማሪዎች ተሳትፈዋል።
የሰላም ሚኒስትር ዴእታ ወይዘሮ አልማዝ መኮነን በኮንፈረንሱ ላይ፥ ሀገራችን ከበርካታ ብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች ውህደት የተገነባች በመሆኗ አንዳችን ላንዳችን ዘብ በመቆም አለኝታነታችንን ማረጋገጥና ወገንተኝነታችንን ማስመስከር ይገባናል ብለዋል።
የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ፕሬዚዳንት ፕሮፌሰር ጣሰው ወልደሀና በበኩለቸው፥ ህብረተሰቡም ሆነ ፖለቲከኞች ዩኒቨርስቲዎች የተለያዩ የምርምር ማእከሎች የመልካም ዜጋ መፍለቂያዎች እንዲሆኑ ከየትኛዉም ጫና ሊታደጓቸው እንደሚገባ ጥሪ አቅርበዋል።

Write a Reply or Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *