loading
የሰላም ሚኒስትሯ የሲዳማና የወላይታ አባቶችን አመሰገኑ

የሰላም ሚኒስትሯ የሲዳማና የወላይታ አባቶችን አመሰገኑ

አርትስ 10/03/2011

 ትናንት “ፍቅር በደልን አይቆጥርም ” በሚል መርህ  በሲዳማና በወላይታ ሕዝቦች መካከል ያለውን ትስስር ለማጠናከር የሚያግዝ የዕርቅና የሰላም ኮንፈረንስ በሀዋሳ ከተማ በሲዳማ ባህል አዳራሽ ተካሂዷል።

በኮንፈረንሱ ላይ  የተገኙት የደኢህዴን ሊቀ መንበርና የኢፌደሪ የሠላም ሚኒስቴር ሚኒስትሯ ወይዘሮ ሙፈሪሀት ካሚል፥ በሲዳማና በወላይታ ሕዝቦች መካከል ሰላም ሰፍኖ  ዕርቅና የሠላም ኮንፈረንስ እንዲካሄድ ትልቅ አስተዋፅኦ የነበራቸውን አባቶች አመስግነዋል፡፡

ሰላም በእያንዳንዳችን ልቦና እና ቤት የሚገኝ በኛው ጥበቃ የሚጎለብት በመሆኑ ልንጠብቀው ይገባል ሲሉም ተናግረዋል፡፡ ወጣቶች ሰላምን ከሚያደፈርሱ ቆስቋሽ ድርጊቶች እንዲጠበቁም አሳስበዋል፡፡

በዕርቁ ሥነ ሥርዓት ላይ ከሲዳማና ወላይታ ዞን የተወጣጡ የኃይማኖት መሪዎችና አባቶች፣ ከሁለቱም ዞኖች የተወጣጡ የባህል ሽማግሌዎችና ወጣቶች፣ የመንግስት ኃላፊዎች፣ የኦሮሞ አባ ገዳዎች እና ጥሪ የተደረገላቸዉ ተጋባዥ እንግዶች ተገኝተዋል፡፡

 

Write a Reply or Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *