loading
የቤጉህዴፓ ፓርቲ ሊቀመንበር መልቀቂያ አስገቡ

አርትስ 18/04/2011

የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ህዝቦች ዴሞክራሲዊ ፓርቲ (ቤጉህዴፓ) ሊቀመንበር አቶ አበራ ባዬታ ትናንት መልቀቂያ አስገብተዋል ተብሏል::

ይህንኑ ተከትሎ የፖርቲው ማዕከላዊ ኮሚቴ በዛሬው ዕለት አስቸኳይ ጉባኤ ያካሄዳል፡፡

የፓርቲው ሊቀመንበር አቶ አበራ ባዬታ ለኢቢሲ እንዳስታወቁት ማዕከላዊ ኮሚቴው በሚያደርገው ጉባዔ የመልቀቂያ ጥያቄውን መርምሮውሳኔ መስጠት ዋነኛ አጀንዳው ይሆናል፡፡

ለፓርቲው ተተኪ ሊቀመንበር መምረጥና በተጓደሉ ሥራ አስፈጻሚዎች አባላት ምትክ ምርጫ እንደሚካሄድም ገልጸዋል::

Write a Reply or Comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *